
ባሕር ዳር፤ የካቲት 26/2017 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ባለፉት ሰባት ወራት ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ መቅረቡን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
በኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ ከተደረገ በኋላ በተለይም የወጭና ገቢ ምርቶችን ሚዛን ለመጠበቅ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑ ይታወቃል።
በዚህም መሰረት የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች በብዛትና በጥራት ለውጭ ገበያ እየቀረቡ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
በአማራ ክልል ባለፉት ሰባት ወራት ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት፤ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ መቅረቡ ተገልጿል።
በአማራ ክልል የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የሰብልና የኢንዱስትሪ ምርቶች ግብይት ዳይሬክተር፤ አቶ ልንገረው አበሻ፤ በበጀት ዓመቱ ከ5 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ለገበያ ለማቅረብ ግብ መያዙን አስታውሰዋል።
በዚህም መሰረት ባለፉት ሰባት ወራት ብቻ ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ ቀርቦ ከ215 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል።
ለውጭ ገበያ ከቀረቡት ምርቶች መካከልም የሰሊጥ፣ የማሾ፣ የአኩሪ አተርና የቦሎቄ ምርቶች መሆናቸውን ዘርዝረዋል።
ከገበሬው እስከ ገበያ መዳረሻዎች ጥራቱን በጠበቀ አግባብ ተመርቶ ለገበያ እንዲቀርብ ለማድረግ የተደረገው ጥረት ውጤት ማምጣቱንም ተናግረዋል።
በባለፈው በጀት ዓመት ከክልሉ በምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ ከቀረበ 3 ሚሊዮን 910 ሺህ ኩንታል የቅባት እህል 478 ሚሊዮን ዶላር መገኘቱም ታውቋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026