የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ ቀርቧል</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

ባሕር ዳር፤ የካቲት 26/2017 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ባለፉት ሰባት ወራት ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ መቅረቡን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ ከተደረገ በኋላ በተለይም የወጭና ገቢ ምርቶችን ሚዛን ለመጠበቅ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑ ይታወቃል።

በዚህም መሰረት የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች በብዛትና በጥራት ለውጭ ገበያ እየቀረቡ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ።

በአማራ ክልል ባለፉት ሰባት ወራት ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት፤ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ መቅረቡ ተገልጿል።

በአማራ ክልል የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የሰብልና የኢንዱስትሪ ምርቶች ግብይት ዳይሬክተር፤ አቶ ልንገረው አበሻ፤ በበጀት ዓመቱ ከ5 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ለገበያ ለማቅረብ ግብ መያዙን አስታውሰዋል።

በዚህም መሰረት ባለፉት ሰባት ወራት ብቻ ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ ቀርቦ ከ215 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል።

ለውጭ ገበያ ከቀረቡት ምርቶች መካከልም የሰሊጥ፣ የማሾ፣ የአኩሪ አተርና የቦሎቄ ምርቶች መሆናቸውን ዘርዝረዋል።

ከገበሬው እስከ ገበያ መዳረሻዎች ጥራቱን በጠበቀ አግባብ ተመርቶ ለገበያ እንዲቀርብ ለማድረግ የተደረገው ጥረት ውጤት ማምጣቱንም ተናግረዋል።

በባለፈው በጀት ዓመት ከክልሉ በምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ ከቀረበ 3 ሚሊዮን 910 ሺህ ኩንታል የቅባት እህል 478 ሚሊዮን ዶላር መገኘቱም ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026