
ባሕር ዳር፤ የካቲት 26/2017 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ባለፉት ሰባት ወራት ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ መቅረቡን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
በኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ ከተደረገ በኋላ በተለይም የወጭና ገቢ ምርቶችን ሚዛን ለመጠበቅ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑ ይታወቃል።
በዚህም መሰረት የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች በብዛትና በጥራት ለውጭ ገበያ እየቀረቡ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
በአማራ ክልል ባለፉት ሰባት ወራት ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት፤ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ መቅረቡ ተገልጿል።
በአማራ ክልል የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የሰብልና የኢንዱስትሪ ምርቶች ግብይት ዳይሬክተር፤ አቶ ልንገረው አበሻ፤ በበጀት ዓመቱ ከ5 ነጥብ 6 ሚሊዮን ኩንታል የቅባትና የጥራጥሬ ምርቶችን ለገበያ ለማቅረብ ግብ መያዙን አስታውሰዋል።
በዚህም መሰረት ባለፉት ሰባት ወራት ብቻ ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባትና የጥራጥሬ ምርት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ ቀርቦ ከ215 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል።
ለውጭ ገበያ ከቀረቡት ምርቶች መካከልም የሰሊጥ፣ የማሾ፣ የአኩሪ አተርና የቦሎቄ ምርቶች መሆናቸውን ዘርዝረዋል።
ከገበሬው እስከ ገበያ መዳረሻዎች ጥራቱን በጠበቀ አግባብ ተመርቶ ለገበያ እንዲቀርብ ለማድረግ የተደረገው ጥረት ውጤት ማምጣቱንም ተናግረዋል።
በባለፈው በጀት ዓመት ከክልሉ በምርት ገበያ በኩል ለውጭ ገበያ ከቀረበ 3 ሚሊዮን 910 ሺህ ኩንታል የቅባት እህል 478 ሚሊዮን ዶላር መገኘቱም ታውቋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026