የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

<p>ኢትዮጵያ የቱሪዝም ኢንዱስትሪዋን በበርሊን ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ኤክስፖ ላይ እያስተዋወቀች ነው</p>

Mar 5, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 25/2017 (ኢዜአ) ፦ኢትዮጵያ የቱሪዝም ኢንዱስትሪዋን በ ' አይ ቲ ቢ' በርሊን 2025 ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ኤክስፖ(ITB) ላይ እያስተዋወቀች ትገኛለች።


ጎብኚዎች የኢትዮጵያን የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎች እና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ስራዎች እየጎበኙ ይገኛል።


በቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ የተመራው እና በቱሪዝም ሥራ ላይ የተሰማሩ አካላት እና የኢትዮጵያ አየር መንገድን ያቀፈው የኢትዮጵያ ልዑክ በኤክስፖው ላይ ‘ምድረ ቀደምት’ የሚለውን መለያ እና የኢትዮጵያን የቱሪዝም ጸጋዎችን ለጎብኚዎች እያስተዋወቀ ነው።


በተጨማሪም ልዑኩ ከጎብኚዎች እና ከአቻ ተሳታፊ አካላት ጋር የጎንዮሽ መድረኮች፣ የቢዝነስ ልውውጦች እና ውይይቶች ይደርጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.