የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በክልሉ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ውጤት ተገኝቷል- ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር)

Mar 10, 2025

IDOPRESS

ደሴ/ ደብረ ብርሃን ፤ የካቲት 29/2017 (ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ ውጤት እያስገኘ መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የክልሉ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡

''ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል" በሚል መሪ ሃሳብ አለም አቀፍ የሴቶች ቀን በክልል ደረጃ ዛሬ በደሴ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል።


በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የክልሉ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ(ዶ/ር) በበዓሉ ላይ እንደገለጹት ያለ ሴቶች ተሳትፎ የሚረጋገጥ ልማት የለም፡፡

በክልሉ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቅንጅት እየተሰራ ያለው ስራ አበረታችና ተስፋ ሰጪ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል።

ዛሬ በደሴ ከተማ ባደረግነው ጉብኝት ሴቶች በግብርና፣ በአገልግሎት፣ በሌማት ቱርፋትና በሌሎችም ውጤታማ ዘርፎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል፡፡


የአማራ ክልል ሴቶች፣ ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ በበኩላቸው፤ የሴቶችን ሁለተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት በማሳደግ ዘላቂ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ተደራጅተው ብድር በማግኘት በአትክልትና ፍራፍሬ፣ በእንሰሳት እርባታ፣ በማድለብና ሌሎች የሥራ ዘርፎች በማሰማራት ሀብት ማፍራት እንዲችሉ ተደርጓል ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ በዓሉ በሰሜን ሸዋ ዞን በተከበረበት ወቅት የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ምክትል ሃላፊ ወይዘሮ ገበያ ተስፋ፤ የሰሜን ሸዋ የሴቶች የልማት ህብረት አደረጃጀት ውጤታማ እንደሆነ በመስክ ማጋገጣቸውን ተናግረዋል።

ፓርቲው ሴቶችን በስልጠናና ሌሎች ድጋፎች በማበረታታት ወደ አመራርነት እንዲመጡ መስራቱን ገልጸዋል።

በሰሜን ሸዋ ዞን ሴቶች እየተከናወኑ ያሉ የልማት ተግባራት በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ ነው ያሉት ደግሞ የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ምክትል ኮሚሽነር ወይዘሮ ሰርክ አዲስ አታሌ ናቸው።

የዞኑ ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ሃላፊ ወይዘሮ የሮምነሽ ጋሻውጠና በበኩላቸው፤ ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች ሴቶች ተጠቃሚ ናቸው ብለዋል።

በቡልጋ ከተማ የኢንዱስትሪ በባለቤት ወይዘሮ አቻም የለሽ ተስፋሁን በሰጡት አስተያየት፤ በ240 ሚሊዮን ብር ካፒታል የከፈቱት ፋብሪካ ከ70 ሰዎች በላይ የስራ እድል መፍጠራቸውን ገልጸዋል።

በደሴ ከተማ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት የተሰማሩት ወይዘሮ ዚነት ሰይድ፤ በልማት ስራ ተሰማርተው የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ምርት ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በዝግጅቶቹ ላይ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሮች አመራር አባላትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026