አዲስ አበባ፤መጋቢት 1/2017 (ኢዜአ)፦በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሀኑ ጸጋዬ ከዶራሌ ሁለገብ ወደብ ስራ አስፈጻሚ ጃማ ኢብራሂም ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።
በውይይቱ ላይ የአፈር ማዳባሪያ ኦፕሬሽን ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል።
አምባሳደር ብርሃኑ፥ በዶራሌ ሁለገብ ወደብ እየተሰራ ያለውን የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን አፈጻጸም እና ቀጣይ ስራዎች ዙሪያ ከስራ አስፈጻሚው ጋር ተወያይተዋል።
የአፈር ማዳበሪያ የማጓጓዝ ሂደቱ በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን ኮሚቴ ከጂቡቲ የወደብ ቴክኒካል ኮሚቴ ጋር በሚያደርገው ሳምንታዊ መደበኛ ውይይቶች ላይ የሚነሱ ሀሳቦች ላይ ማብራሪያ ሰጥቷል።
የዶራሌ ሁለገብ ወደብስራ አስፈጻሚ ጃማ ኢብራሂም በዘንድሮ ዓመት በተጀመረው ኦፕሬሽን አማካኝነት ለኢትዮጵያ አርሶ አደሮች ማዳበሪያ በሰዓቱ ለማድረስ የማሽነሪዎች ጥገና፣ የአገልግሎት ጥራት እና ቅልጥፍናን ታሳቢ ያደረገ ስራ መከናወኑን መግለጻቸውን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025