
አዲስ አበባ፤መጋቢት 1/2017 (ኢዜአ)፦በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሀኑ ጸጋዬ ከዶራሌ ሁለገብ ወደብ ስራ አስፈጻሚ ጃማ ኢብራሂም ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።
በውይይቱ ላይ የአፈር ማዳባሪያ ኦፕሬሽን ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል።
አምባሳደር ብርሃኑ፥ በዶራሌ ሁለገብ ወደብ እየተሰራ ያለውን የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን አፈጻጸም እና ቀጣይ ስራዎች ዙሪያ ከስራ አስፈጻሚው ጋር ተወያይተዋል።
የአፈር ማዳበሪያ የማጓጓዝ ሂደቱ በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን ኮሚቴ ከጂቡቲ የወደብ ቴክኒካል ኮሚቴ ጋር በሚያደርገው ሳምንታዊ መደበኛ ውይይቶች ላይ የሚነሱ ሀሳቦች ላይ ማብራሪያ ሰጥቷል።
የዶራሌ ሁለገብ ወደብስራ አስፈጻሚ ጃማ ኢብራሂም በዘንድሮ ዓመት በተጀመረው ኦፕሬሽን አማካኝነት ለኢትዮጵያ አርሶ አደሮች ማዳበሪያ በሰዓቱ ለማድረስ የማሽነሪዎች ጥገና፣ የአገልግሎት ጥራት እና ቅልጥፍናን ታሳቢ ያደረገ ስራ መከናወኑን መግለጻቸውን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025