
አዲስ አበባ፤መጋቢት 1/2017 (ኢዜአ)፦በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሀኑ ጸጋዬ ከዶራሌ ሁለገብ ወደብ ስራ አስፈጻሚ ጃማ ኢብራሂም ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።
በውይይቱ ላይ የአፈር ማዳባሪያ ኦፕሬሽን ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል።
አምባሳደር ብርሃኑ፥ በዶራሌ ሁለገብ ወደብ እየተሰራ ያለውን የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን አፈጻጸም እና ቀጣይ ስራዎች ዙሪያ ከስራ አስፈጻሚው ጋር ተወያይተዋል።
የአፈር ማዳበሪያ የማጓጓዝ ሂደቱ በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን ኮሚቴ ከጂቡቲ የወደብ ቴክኒካል ኮሚቴ ጋር በሚያደርገው ሳምንታዊ መደበኛ ውይይቶች ላይ የሚነሱ ሀሳቦች ላይ ማብራሪያ ሰጥቷል።
የዶራሌ ሁለገብ ወደብስራ አስፈጻሚ ጃማ ኢብራሂም በዘንድሮ ዓመት በተጀመረው ኦፕሬሽን አማካኝነት ለኢትዮጵያ አርሶ አደሮች ማዳበሪያ በሰዓቱ ለማድረስ የማሽነሪዎች ጥገና፣ የአገልግሎት ጥራት እና ቅልጥፍናን ታሳቢ ያደረገ ስራ መከናወኑን መግለጻቸውን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026