የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ ከዶራሌ ሁለገብ ወደብ ስራ አስፈጻሚ ጋር ተወያዩ

Mar 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 1/2017 (ኢዜአ)፦በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብርሀኑ ጸጋዬ ከዶራሌ ሁለገብ ወደብ ስራ አስፈጻሚ ጃማ ኢብራሂም ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።


በውይይቱ ላይ የአፈር ማዳባሪያ ኦፕሬሽን ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል።


አምባሳደር ብርሃኑ፥ በዶራሌ ሁለገብ ወደብ እየተሰራ ያለውን የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን አፈጻጸም እና ቀጣይ ስራዎች ዙሪያ ከስራ አስፈጻሚው ጋር ተወያይተዋል።


የአፈር ማዳበሪያ የማጓጓዝ ሂደቱ በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።


የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን ኮሚቴ ከጂቡቲ የወደብ ቴክኒካል ኮሚቴ ጋር በሚያደርገው ሳምንታዊ መደበኛ ውይይቶች ላይ የሚነሱ ሀሳቦች ላይ ማብራሪያ ሰጥቷል።


የዶራሌ ሁለገብ ወደብስራ አስፈጻሚ ጃማ ኢብራሂም በዘንድሮ ዓመት በተጀመረው ኦፕሬሽን አማካኝነት ለኢትዮጵያ አርሶ አደሮች ማዳበሪያ በሰዓቱ ለማድረስ የማሽነሪዎች ጥገና፣ የአገልግሎት ጥራት እና ቅልጥፍናን ታሳቢ ያደረገ ስራ መከናወኑን መግለጻቸውን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026