አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፦ የሀገር ውስጥ ገቢ የመሰብሰብ አቅምን ማሳደግ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ኮንፍረንስ ከነገ ጀምሮ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።
ኮንፍረንሱ "የልማት ግቦችን ለመደገፍ የሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን ማጎልበት" በሚል መሪ ሀሳብ ይካሄዳል።
የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) እና የአይኤምኤፍ ቀጣናዊ የቴክኒክ ድጋፍ ማዕከል የምስራቅ አፍሪካ ቢሮ(አፍሪታክ) ስብሰባውን በጋራ ያዘጋጁ ተቋማት ናቸው።
በኮንፍረንሱ ላይ የገቢዎች ሚኒስቴር እና የገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ ኃላፊዎችን ጨምሮ ከ11 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የተወከሉ የገቢው ዘርፍ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የሚመለከታቸው የገቢና ፋይናንስ ባለሙያዎችና አማካሪዎች እንዲሁም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ይገኛሉ።
የኮንፍንሱ ዋና ዓላማ የልማት ግቦችን መደገፍ የሚያስችልና የሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን ለማጎልበት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ለመምከር ያተኮረ ነው።
ቀጣናዊ ኮንፍረንሱ እስከ መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይም የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
ከሁነቱ ጎን ለጎን የተሳታፊዎች የጉብኝት መርሃ ግብር ይካሄዳል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025