
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፦ የሀገር ውስጥ ገቢ የመሰብሰብ አቅምን ማሳደግ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ኮንፍረንስ ከነገ ጀምሮ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።
ኮንፍረንሱ "የልማት ግቦችን ለመደገፍ የሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን ማጎልበት" በሚል መሪ ሀሳብ ይካሄዳል።
የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) እና የአይኤምኤፍ ቀጣናዊ የቴክኒክ ድጋፍ ማዕከል የምስራቅ አፍሪካ ቢሮ(አፍሪታክ) ስብሰባውን በጋራ ያዘጋጁ ተቋማት ናቸው።
በኮንፍረንሱ ላይ የገቢዎች ሚኒስቴር እና የገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ ኃላፊዎችን ጨምሮ ከ11 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የተወከሉ የገቢው ዘርፍ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የሚመለከታቸው የገቢና ፋይናንስ ባለሙያዎችና አማካሪዎች እንዲሁም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ይገኛሉ።
የኮንፍንሱ ዋና ዓላማ የልማት ግቦችን መደገፍ የሚያስችልና የሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን ለማጎልበት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ለመምከር ያተኮረ ነው።
ቀጣናዊ ኮንፍረንሱ እስከ መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይም የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
ከሁነቱ ጎን ለጎን የተሳታፊዎች የጉብኝት መርሃ ግብር ይካሄዳል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026