አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልልን ግብርና ማሸጋገር ሀገራዊ የብልፅግና ግባችንን ለማሳካት ትልቅ አቅም ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ የክልሉን ግብርና ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ በተዘጋጀው የአስር ዓመት የመነሻ ዕቅድ ላይ ከምሁራንና ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይተናል ብለዋል።
ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ በየክልሎቻችን የሚገኙ የግብርና እምቅ ፀጋዎችን፣ ሀገር በቀል ፖሊሲና አቅሞቻችንን አሟጠን መጠቀም ላይ ትኩረት ሰጥተን እየሰራን እንገኛለን ሲሉም ገልጸዋል፡፡
ይህንን እምቅ ፀጋ ለይቶ ለልማት በማዋል እና የክልሉን የመልማት አቅም በማባዛት፣ ሀገርን ከድህነት ለማላቀቅ ትጋት፣ ትኩረትና መናበብን ይፈልጋል ነው ያሉት።
በመሆኑም ዕቅዱን ከሀገራዊ ግቦቻችን ጋር በተናበበ መልኩ ለማስፈጸም የሥራ ባህልና የአመለካከት ለውጥ ወሳኝ በመሆኑ ሁሉም በተነሳሽነትና በቁጭት ሊሠራ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025