የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የአማራ ክልልን ግብርና ማሸጋገር ሀገራዊ የብልፅግና ግባችንን ለማሳካት ትልቅ አቅም ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Mar 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልልን ግብርና ማሸጋገር ሀገራዊ የብልፅግና ግባችንን ለማሳካት ትልቅ አቅም ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ የክልሉን ግብርና ትራንስፎርሜሽን ለማረጋገጥ በተዘጋጀው የአስር ዓመት የመነሻ ዕቅድ ላይ ከምሁራንና ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይተናል ብለዋል።


ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ በየክልሎቻችን የሚገኙ የግብርና እምቅ ፀጋዎችን፣ ሀገር በቀል ፖሊሲና አቅሞቻችንን አሟጠን መጠቀም ላይ ትኩረት ሰጥተን እየሰራን እንገኛለን ሲሉም ገልጸዋል፡፡

ይህንን እምቅ ፀጋ ለይቶ ለልማት በማዋል እና የክልሉን የመልማት አቅም በማባዛት፣ ሀገርን ከድህነት ለማላቀቅ ትጋት፣ ትኩረትና መናበብን ይፈልጋል ነው ያሉት።

በመሆኑም ዕቅዱን ከሀገራዊ ግቦቻችን ጋር በተናበበ መልኩ ለማስፈጸም የሥራ ባህልና የአመለካከት ለውጥ ወሳኝ በመሆኑ ሁሉም በተነሳሽነትና በቁጭት ሊሠራ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025