የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ የ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን የጅቡቲ ፍራንክ ቦንድ ግዢ ፈጸመ

Mar 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፦በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ የ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን የጅቡቲ ፍራንክ ቦንድ ግዢ ፈጽሟል።

በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኮሚዩኒቲ ማህበር ስራ አስፈጻሚ አመራሮች ክቡር አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ በተገኙበት የቦንድ ግዢውን አስረክበዋል።


ኮሚዩኒቲው ከዚህ ቀደም በአገራችን ለሚደረጉ የተለያዩ የልማት ጥሪዎች እና ማህበራዊ ድጋፎች ህዝቡን በማስተባበር ትልቅ ተሳትፎ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

ዘንድሮም የ2 ነጥብ7 ሚሊየን የጅቡቲ ፍራንክ የቦንድ ግዥ ለአምባሳደሩ በማስረከብ ድጋፋቸውን መግለጻቸውን ከኤምባሲው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.