የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በአማራ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማቶችን የማሻሻል ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

Mar 12, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማቶችን የማሻሻል ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ መንገድ ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ኃላፊ ጋሻው አወቀ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ የሚገኙ የመንገድ መሰረተ ልማቶችን የማሻሻል ስራ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

በክልሉ ከአንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የ95 ድልድዮች ግንባታ መጀመሩን ገልጸው በክልሉ ዞኖችን፣ ወረዳዎችንና ቀበሌዎችን ለማገናኘት ከዚህ በፊት በገጠር ተደራሽነት ተሰርተው የነበሩ መንገዶችን እንደሚያሻሽሉ አስረድተዋል።

አዲስ በሚሰሩና እየተሰሩ በሚገኙ መንገዶች መካከል በክልሉ መንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የሚገነቡት እነዚህ ድልድዮች ቀደም ሲል ያጋጥሙ የነበሩ የመንገድ ተደራሽነት ችግሮችን እንደሚያቃልሉም ጠቁመዋል።

መንገዶቹ ክረምት ከበጋ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ ታቅዶ የሚገነቡት ድልድዮች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ክትትል እንደሚደረግባቸውም አስረድተዋል።

ከሚገነቡት ውስጥም 24 ተንጠልጣይ ድልድዮች እንደሆኑ ጠቅሰው፤ ሁሉም ድልድዮች በተያዘው የበጀት ዓመት አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት መታቀዱን አመልክተዋል።

የደቡብ ወሎ ዞን መንገድ መምሪያ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ሐሰን በበኩላቸው፤ በዞኑ የሶስት ድልድዮች ግንባታ መጀመሩንና ከመካከላቸውም ሁለቱ ተንጠልጣይ እንደሆኑ ገልጸዋል።

በተያዘላቸው ጊዜ በጥራት እንዲጠናቀቁ ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.