
ደሴ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማቶችን የማሻሻል ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ መንገድ ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ ጋሻው አወቀ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ የሚገኙ የመንገድ መሰረተ ልማቶችን የማሻሻል ስራ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
በክልሉ ከአንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የ95 ድልድዮች ግንባታ መጀመሩን ገልጸው በክልሉ ዞኖችን፣ ወረዳዎችንና ቀበሌዎችን ለማገናኘት ከዚህ በፊት በገጠር ተደራሽነት ተሰርተው የነበሩ መንገዶችን እንደሚያሻሽሉ አስረድተዋል።
አዲስ በሚሰሩና እየተሰሩ በሚገኙ መንገዶች መካከል በክልሉ መንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የሚገነቡት እነዚህ ድልድዮች ቀደም ሲል ያጋጥሙ የነበሩ የመንገድ ተደራሽነት ችግሮችን እንደሚያቃልሉም ጠቁመዋል።
መንገዶቹ ክረምት ከበጋ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ ታቅዶ የሚገነቡት ድልድዮች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ክትትል እንደሚደረግባቸውም አስረድተዋል።
ከሚገነቡት ውስጥም 24 ተንጠልጣይ ድልድዮች እንደሆኑ ጠቅሰው፤ ሁሉም ድልድዮች በተያዘው የበጀት ዓመት አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት መታቀዱን አመልክተዋል።
የደቡብ ወሎ ዞን መንገድ መምሪያ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ሐሰን በበኩላቸው፤ በዞኑ የሶስት ድልድዮች ግንባታ መጀመሩንና ከመካከላቸውም ሁለቱ ተንጠልጣይ እንደሆኑ ገልጸዋል።
በተያዘላቸው ጊዜ በጥራት እንዲጠናቀቁ ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026