
ደሴ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል የመንገድ መሰረተ ልማቶችን የማሻሻል ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ መንገድ ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ ጋሻው አወቀ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ የሚገኙ የመንገድ መሰረተ ልማቶችን የማሻሻል ስራ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
በክልሉ ከአንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የ95 ድልድዮች ግንባታ መጀመሩን ገልጸው በክልሉ ዞኖችን፣ ወረዳዎችንና ቀበሌዎችን ለማገናኘት ከዚህ በፊት በገጠር ተደራሽነት ተሰርተው የነበሩ መንገዶችን እንደሚያሻሽሉ አስረድተዋል።
አዲስ በሚሰሩና እየተሰሩ በሚገኙ መንገዶች መካከል በክልሉ መንግስትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የሚገነቡት እነዚህ ድልድዮች ቀደም ሲል ያጋጥሙ የነበሩ የመንገድ ተደራሽነት ችግሮችን እንደሚያቃልሉም ጠቁመዋል።
መንገዶቹ ክረምት ከበጋ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ ታቅዶ የሚገነቡት ድልድዮች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ክትትል እንደሚደረግባቸውም አስረድተዋል።
ከሚገነቡት ውስጥም 24 ተንጠልጣይ ድልድዮች እንደሆኑ ጠቅሰው፤ ሁሉም ድልድዮች በተያዘው የበጀት ዓመት አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት መታቀዱን አመልክተዋል።
የደቡብ ወሎ ዞን መንገድ መምሪያ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ሐሰን በበኩላቸው፤ በዞኑ የሶስት ድልድዮች ግንባታ መጀመሩንና ከመካከላቸውም ሁለቱ ተንጠልጣይ እንደሆኑ ገልጸዋል።
በተያዘላቸው ጊዜ በጥራት እንዲጠናቀቁ ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026