ሀዋሳ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራው በተሻለ ፍጥነት ሌት ተቀን እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገለጸ።
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሀዋሳ እየተከናወነ ያለውን የመጀመሪያ ዙር ሁለተኛ ምዕራፍ የኮሪደር ልማት እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል ።
ይህም ከ5 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት እንዳለው ተመልክቷል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ የልማት ሥራው በቀንም በማታም ፈረቃ በተሻለ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
እስከ ሰኔ ወር ባለው ጊዜ አጥጋቢ የሆነ አፈፃፀም ደረጃ ማድረስ ይቻላል ብለዋል፡፡
የኮሪደር ልማቱ ለሀዋሳ ከተማ ተጨማሪ ውበት እያላበሳት መሆኑን ገልጸው፤ በተለይ ይህ ምዕራፍ ከሀዋሳ ሐይቅ አካባቢ ጋር የሚያገናኝ መንገድና ሌሎች የመዝናኛ ሥራዎችን እንደሚያካትት ጠቁመዋል።
ልማቱ ሀዋሳ ይበልጥ ቱሪስቶችን የምትስብ ከተማ ያደርጋታልም ሲሉ ርዕሰ መስተዳደሩ ተናግረዋል፡፡
የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል የመጀመሪያ ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉን አስታውሰዋል።
ከተጠናቀቀው ሥራ ልምድ በመውሰድ በተሻለና ባማረ መልኩ የሁለተኛውን ምዕራፍ ሰርቶ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየሰራን ነው ብለዋል ፡፡
የልማት ሥራው በተሻለ አፈፃፀም እንዲከናወን ዕለት በዕለት ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል ፡፡
ሥራው በሚከናወንበት አካባቢ የሚገኙ ነዋሪዎች የልማቱ አፈጻጸም የተሻለ ደረጃ ላይ እንዲደርስ የበኩላቸውን ድጋፍ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል፡፡
የሥራው ተቋራጭ ይርጋዓለም ኮንስትራክሽን ባለቤት ኢንጂነር ዘላለም ወልደአማኑኤል፤ የኮሪደር ልማቱ የአስፋልት ፣ የእግረኛ፣ የብስክሌት መንገድና ሌሎችም ሥራዎችን ያካተተ መሆኑንና በተያዘለት ጊዜና ጥራቱን ጠብቆ እንደሚከናወን ገልጸዋል።
በአሁን ወቅት በከፊል የአስፋልት ማንጠፍ ሥራ ለማከናወን እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተያዘለት የጊዜ ገደብ የጥራት ደረጃው እንደተጠበቀ እንዲጠናቀቅ ሌት ተቀን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል ፡፡
በጉብኝቱ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ እና ሌሎችም የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።፡
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025