
ሀዋሳ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦የሀዋሳ ከተማ የኮሪደር ልማት ሥራው በተሻለ ፍጥነት ሌት ተቀን እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገለጸ።
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሀዋሳ እየተከናወነ ያለውን የመጀመሪያ ዙር ሁለተኛ ምዕራፍ የኮሪደር ልማት እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል ።
ይህም ከ5 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት እንዳለው ተመልክቷል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ የልማት ሥራው በቀንም በማታም ፈረቃ በተሻለ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
እስከ ሰኔ ወር ባለው ጊዜ አጥጋቢ የሆነ አፈፃፀም ደረጃ ማድረስ ይቻላል ብለዋል፡፡
የኮሪደር ልማቱ ለሀዋሳ ከተማ ተጨማሪ ውበት እያላበሳት መሆኑን ገልጸው፤ በተለይ ይህ ምዕራፍ ከሀዋሳ ሐይቅ አካባቢ ጋር የሚያገናኝ መንገድና ሌሎች የመዝናኛ ሥራዎችን እንደሚያካትት ጠቁመዋል።
ልማቱ ሀዋሳ ይበልጥ ቱሪስቶችን የምትስብ ከተማ ያደርጋታልም ሲሉ ርዕሰ መስተዳደሩ ተናግረዋል፡፡

የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል የመጀመሪያ ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉን አስታውሰዋል።
ከተጠናቀቀው ሥራ ልምድ በመውሰድ በተሻለና ባማረ መልኩ የሁለተኛውን ምዕራፍ ሰርቶ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየሰራን ነው ብለዋል ፡፡
የልማት ሥራው በተሻለ አፈፃፀም እንዲከናወን ዕለት በዕለት ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል ፡፡
ሥራው በሚከናወንበት አካባቢ የሚገኙ ነዋሪዎች የልማቱ አፈጻጸም የተሻለ ደረጃ ላይ እንዲደርስ የበኩላቸውን ድጋፍ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል፡፡
የሥራው ተቋራጭ ይርጋዓለም ኮንስትራክሽን ባለቤት ኢንጂነር ዘላለም ወልደአማኑኤል፤ የኮሪደር ልማቱ የአስፋልት ፣ የእግረኛ፣ የብስክሌት መንገድና ሌሎችም ሥራዎችን ያካተተ መሆኑንና በተያዘለት ጊዜና ጥራቱን ጠብቆ እንደሚከናወን ገልጸዋል።
በአሁን ወቅት በከፊል የአስፋልት ማንጠፍ ሥራ ለማከናወን እየተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተያዘለት የጊዜ ገደብ የጥራት ደረጃው እንደተጠበቀ እንዲጠናቀቅ ሌት ተቀን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል ፡፡
በጉብኝቱ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንታዬ ከበደ እና ሌሎችም የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።፡
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025