
የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያና ልዩ ትኩረት ይሰጣል። ለቀጣናዊ ትስስር፣ ለጋራ እድገትና ተጠቃሚነት ትኩረት መስጠት የዲፕሎማሲዋ አስኳል ነው።
ከቀጣናው ሀገራት ጋር ካሉ የትብብር መስኮች መካከል በኃይል መሰረተ ልማት መተሳሰር አንዱ መሆኑም ይታወቃል።
ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት የምታቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል የሀገራቱን ኢኮኖሚያዊ ትብብርን የሚያጠናክር እና የኢትዮጵያን ቀጣናውን በመሰረተ ልማት የማስተሳሰር ጽኑ ፍላጎት ማሳያ ነው።
በተጨማሪም በቀጣናው ዘላቂ የኤሌክትሪክ ገበያ ልማትን ማረጋገጥ የሚያስችል ክፍለ አሕጉራዊ ጥረትም እንደሆነ ይታወቃል።
ኢትዮጵያ፣ ታንዛንያ እና ኬንያ የሶስትዮሽ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ስምምነት በጥር ወር 2017 ዓ.ም መፈራረማቸው ይታወሳል።
የሶስትዮሽ ስምምነቱ ኢትዮጵያ ከታንዛኒያ ጋር የኃይል ሽያጭ እንዲሁም ኬንያ ከታንዛንያ ጋር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ኪራይ ውልን ያካተተ ነው።
በሥምምነቱ መሰረት ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ 100 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ የምታከናውን ሲሆን
የኃይል ሽያጭ ሥምምነቱ በሀገራቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ፀድቆ ከሚያዝያ 2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ ይጠበቃል።

የታንዛንያ የኤሌክትሪክ አቅራቢ ኩባንያ(TANESCO) በኬንያ በኩል ከኢትዮጵያ ከሚገዛው የኤሌክትሪክ ኃይል በዓመት 32 ቢሊዮን የታንዛንያ ሽልንግ (ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ) ወጪ እንደሚድን መግለጹን የሀገሪቱ ጋዜጣ ዴይሊ ኒውስ ዘገባ ያመለክታል።
ይህም በታንዛንያ በተለይም በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል ያለውን የኃይል ብክነት ለመቀነስ እና የተሻለ የኤሌክትሪክ ስርጭት እንዲኖር ያስችላል ነው የተባለው።
የታንዛንያ መንግስት ዋና ቃል አቀባይ ጌርሰን ምሲግዋ ታንዛንያ አብዛኛውን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦቷን ከደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል እንደምታገኝ ይገልጻሉ።
በዚህም ምክንያት የኃይል አቅርቦቱን ለማድረስ ረጅም ርቀት እንደሚፈጅና የሚባክነው የኢነርጂ መጠን ሀገሪቱን በየዓመቱ በቢሊዮኖች የሚቆጠር የታንዛንያ ሽልንግ እንደሚያሳጣት አመልክተዋል።
ይህን ተከትሎ ታንዛንያ ከምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት ስርዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት ወስናለች።
ታንዛንያ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የምታገኝበት ዋጋ ተመጣጣኝ እንደሆነ እና የኃይል ብክነት እና መቆራረጥን ለመቀነስ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ነው ዴይሊ ኒውስ በዘገባው ያሰፈረው።
ይህ ስምምነት የታንዛንያ ብሔራዊ የኃይል ቋትን እንደሚያረጋጋም ታምኖበታል።
የታንዛንያ መንግስት ዋና ቃል አቀባይ ጌርሰን ምሲግዋ ከዚህ ቀደም ታንዛንያ ከዛምቢያ፣ ዩጋንዳ እና ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ትገዛ እንደነበር አስታውሰዋል።
ታንዛንያ ከኢትዮጵያ የምትገዛው የኤሌክትሪክ ኃይል ከምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት መተሳሳር ጋር ተዳምሮ የኢኒርጂ ዘርፏን ለማሻሻል እና ለኢኮኖሚ እድገቷ የሚያግዝ ተአማኒነት ያለው የኃይል አቅርቦት እንዲኖራት አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ በዘገባው ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ታንዛንያ የተፈራሙት ስምምነት ለቀጣናዊ የንግድና ኢኮኖሚ ትስስር ጉልህ ፋይዳ አለው።
የምስራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኅይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት በታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም መጀመሩ የሚታወስ ነው።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026