
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን እና መልቲቾይስ አፍሪካ በኪነጥበብ ዘርፍ ፈጠራዎች የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ ዙሪያ በጋራ ለመስራት የሶስትዮሽ ትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የኪነጥበብና ስነጥበብ ፈጠራ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልመህዲ ስምምነቱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት ኪነ-ጥበብና ስነ-ጥበብ ድንበር የሌለው የሰው ልጅ የፈጠራ ውጤት መሆኑን ገልጸዋል።
በጊዜና በሁኔታ የማይወሰኑ ዘመን የተሻገሩ ኪነ-ጥበባዊ ስራዎች ቢኖሩም የኪነጥበቡ ባለቤቶች በቅጅና ተዛማጅ መብቶቻቸው በተገቢው መንገድ ተጠቃሚ ሲሆኑ አይስተዋልም ብለዋል።
ይህም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በ2010 ዓ.ም ፀድቆ ስራ ላይ በዋለው የፊልም ፖሊሲ ካስቀመጣቸው ቁልፍ የፖሊሲ ማስፈፀሚያ ስትራቴጂዎች መካከል አንዱ የፈጠራ፣ የቅጂና ተዛማጅ መብቶች ጥሰትን መከላከል አንዱ መሆኑን አንስተዋል።
ለቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ ከሚሰሩ አካላት ጋር በትብብር ለመስራት የዛሬው የሶስትዮሽ ትብብር ስምምነት አንዱ ማሳያ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር እንዳሉ ሞሲሳ በበኩላቸው የኪነ ጥበብ ስራዎች የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥሰት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መምጣት የሚቀርቡ የፈጠራ ስራዎችን ጥራት አጓድሏል ነው ያሉት።
በተጨማሪም የዘርፉ ሙያተኞችና ተቋማትን ዘላቂ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ድጋፍ እንዲያጡ እያደረገ ለስነ-ልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እያስከተለ በመሆኑ በጋራ መስራት የችግሩ መፍተሔ እንድንሆን ያስችላል ብለዋል።

የመልቲቾይስ አፍሪካ ግሩፕ የቁጥጥርና ኮርፖሬት ጉዳዮች ሀላፊ ኪያቤትስዌ ሞዲሞንግ(ዶ/ር) በበኩላቸው የኪነጥበቡ ባለቤቶች ተገቢውን የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የአፍሪካ ተሞክሮችን በመውሰድ ለችግሩ መፍተሔ መስጠት አስፈላጊ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የሚገኘው የበየነ መረብና የቴክኖሎጂ መስፋፋት የሰጠውን ጠቀሜታ ያህል በቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ በኩል ለባለሙያውና ለኢንቨስተሩ ፈታኝ በመሆኑ የጋራ ስምምነቱ የመፍተሔ አካል እንደሚሆን ተናግረዋል።
የሶስትዮሽ የትብብር ስምምነቱ ትኩረት ግንዛቤ ለመፍጠር፣ የህግ ማሻሻያ ለማድረግ፣ መብትን ለማስጠበቅ፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ህግና ስርአት ለማበጀት፣ የቴሌኮም ካምፓኒዎችን አሰራር ለማስተካከል፣ የፈጠራ ባለቤቶችን ተጠቃሚ ለማድረግና የአፍሪካን ልምድ ለመቅሰም እንደሆነ በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026