
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2017(ኢዜአ)፡- 57ኛው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የፋይናንስ፣ምጣኔ ሃብትና ፕላን ሚኒስትሮች ጉባኤ በባለሙያዎች ደረጃ ዛሬ መካሄድ ይጀምራል።
ጉባዔው “ የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን ማፋጠን፤ አፈጻጸሙን የሚያልቁ ስትራቴጂካዊ እርምጃዎችን መቀየስ” በሚል መሪ ሀሳብ ይከናወናል።
የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራ የእስከ አሁን አፈጻጸም እና ቀጣይ ስራዎች የጉባዔው ዋንኛ አጀንዳ መሆኑን ኢዜአ ከኢሲኤ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ዲጂታላይዜሽን፣ የምግብ ዋስትና እና የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽን ሌሎች የጉባዔው የመወያያ ርዕሰ ጉዳዮች ናቸው።
57ኛው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የፋይናንስ፣ ምጣኔ ሃብትና ፕላን ሚኒስትሮች ጉባኤ በባለሙያዎች ደረጃ ከመጋቢት 3 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ይካሄዳል።
ጉባዔው በሚኒስትሮች ደረጃ መጋቢት 8 እና 9 ቀን 2017 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን በጉባዔው መሪ ሀሳብ ላይ ከፍተኛ የፖሊሲ ምክክር መድረክ ያደርጋሉ።
በተጨማሪም ከጉባዔው ጋር የተጓዳኙ የተለያዩ ሁነቶች እንደሚደረጉም ኢሲኤ አስታውቋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026