የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የፋይናንስና ምጣኔ ሃብት ሚኒስትሮች ጉባኤ ዛሬ ይጀመራል

Mar 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2017(ኢዜአ)፡- 57ኛው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የፋይናንስ፣ምጣኔ ሃብትና ፕላን ሚኒስትሮች ጉባኤ በባለሙያዎች ደረጃ ዛሬ መካሄድ ይጀምራል።

ጉባዔው “ የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን ማፋጠን፤ አፈጻጸሙን የሚያልቁ ስትራቴጂካዊ እርምጃዎችን መቀየስ” በሚል መሪ ሀሳብ ይከናወናል።

የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራ የእስከ አሁን አፈጻጸም እና ቀጣይ ስራዎች የጉባዔው ዋንኛ አጀንዳ መሆኑን ኢዜአ ከኢሲኤ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ዲጂታላይዜሽን፣ የምግብ ዋስትና እና የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽን ሌሎች የጉባዔው የመወያያ ርዕሰ ጉዳዮች ናቸው።

57ኛው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) የፋይናንስ፣ ምጣኔ ሃብትና ፕላን ሚኒስትሮች ጉባኤ በባለሙያዎች ደረጃ ከመጋቢት 3 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ይካሄዳል።

ጉባዔው በሚኒስትሮች ደረጃ መጋቢት 8 እና 9 ቀን 2017 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን በጉባዔው መሪ ሀሳብ ላይ ከፍተኛ የፖሊሲ ምክክር መድረክ ያደርጋሉ።

በተጨማሪም ከጉባዔው ጋር የተጓዳኙ የተለያዩ ሁነቶች እንደሚደረጉም ኢሲኤ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026