የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ለውጭ ባለሀብቶች ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታ ለመፍጠር የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል

Mar 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 5/2017 (ኢዜአ)፦መንግስት ለውጭ ባለሀብቶች ምቹ ስነ ምህዳር ለመፍጠር የጀመረውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።


የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሶስትዮሽ ውይይት አድርገዋል።


ውይይቱ የውጭ ባለሀብቶች ምቹ እና ሳቢ የኢንቨስትመንት ከባቢ መፍጠር ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው።


በስራ ላይ ለሚገኙ ባለሀብቶች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ተደራሽ ማድረግ እና የውጭ ባለሀብቶች ለሚገጥሟቸው ችግሮች ፈጣን ምላሽ መስጠት በሚቻልበት ሁኔታ ላይም መክረዋል።


በተደጋጋሚ የኃይል አቅርቦት ችግር በገጠማቸው የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ዘላቂ መፍትሄ ለማበጀት ከባለሀብቶች ጋር ያለውን የትብብር ስራ ለማጠናከር ከስምንት ላይ ተደርሷል።


ኮሚሽኑ በቀጣይነትም ለውጭ ባለሀብቶች ምቹ፣ አስቻይ እና ግልፅ የኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚያደርገውን ቅንጅታዊ አሰራር እና ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.