
አዲስ አበባ፤መጋቢት 5/2017 (ኢዜአ)፦መንግስት ለውጭ ባለሀብቶች ምቹ ስነ ምህዳር ለመፍጠር የጀመረውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሶስትዮሽ ውይይት አድርገዋል።
ውይይቱ የውጭ ባለሀብቶች ምቹ እና ሳቢ የኢንቨስትመንት ከባቢ መፍጠር ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው።
በስራ ላይ ለሚገኙ ባለሀብቶች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ተደራሽ ማድረግ እና የውጭ ባለሀብቶች ለሚገጥሟቸው ችግሮች ፈጣን ምላሽ መስጠት በሚቻልበት ሁኔታ ላይም መክረዋል።
በተደጋጋሚ የኃይል አቅርቦት ችግር በገጠማቸው የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ዘላቂ መፍትሄ ለማበጀት ከባለሀብቶች ጋር ያለውን የትብብር ስራ ለማጠናከር ከስምንት ላይ ተደርሷል።
ኮሚሽኑ በቀጣይነትም ለውጭ ባለሀብቶች ምቹ፣ አስቻይ እና ግልፅ የኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚያደርገውን ቅንጅታዊ አሰራር እና ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክቷል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026