
አዲስ አበባ፤መጋቢት 5/2017 (ኢዜአ)፦መንግስት ለውጭ ባለሀብቶች ምቹ ስነ ምህዳር ለመፍጠር የጀመረውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሶስትዮሽ ውይይት አድርገዋል።
ውይይቱ የውጭ ባለሀብቶች ምቹ እና ሳቢ የኢንቨስትመንት ከባቢ መፍጠር ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው።
በስራ ላይ ለሚገኙ ባለሀብቶች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ተደራሽ ማድረግ እና የውጭ ባለሀብቶች ለሚገጥሟቸው ችግሮች ፈጣን ምላሽ መስጠት በሚቻልበት ሁኔታ ላይም መክረዋል።
በተደጋጋሚ የኃይል አቅርቦት ችግር በገጠማቸው የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ዘላቂ መፍትሄ ለማበጀት ከባለሀብቶች ጋር ያለውን የትብብር ስራ ለማጠናከር ከስምንት ላይ ተደርሷል።
ኮሚሽኑ በቀጣይነትም ለውጭ ባለሀብቶች ምቹ፣ አስቻይ እና ግልፅ የኢንቨስትመንት ከባቢ ለመፍጠር ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚያደርገውን ቅንጅታዊ አሰራር እና ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመልክቷል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025