
ዲላ፤መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴው ግድብ ግንባታ ከ179 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ የሕዳሴው ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ገለጸ።
በክልሉ በቀጣይ ህዝባዊ ተሳትፎን በማጠናከር ገቢን ለማሳደግ በየደረጃው የንቅናቄ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑም ተመላክቷል።
የጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ዘርፉ አጥናፉ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የክልሉ ህዝብ ለሕዳሴው ግድብ የቦንድ ግዥ በመፈጸም ድጋፉን እያጠናከረና አሻራውን እያሳረፈ ይገኛል ።
በተለይ የሕዳሴው ግድብ ዋንጫ ወደ ክልሉ መምጣትን ተከትሎ በተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች ዋንጫውን በማዘዋወር የገቢ ማሰባሰብ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በተያዘው ዓመት ያለፉት ስድስት ወራት በቦንድ ግዥና በስጦታ ከ179 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።
በክልሉ ዘንድሮ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ ነው" ያሉት ሃላፊው በቀጣይ ወራት የህብረተሰቡን ተሳትፎ በማጠናከር ዕቅዱን ለማሳካት በየደረጃው የንቅናቄ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአንድነታችን ማሳያና የዛሬው ትውልዱ አድዋ ነው ያሉት አቶ ዘርፉ፣ ህብረተሰቡ በቦንድ ግዥና በተለያየ መንገድ ሲያደርገው የነበረውን ድጋፍ እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026