የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በክልሉ ለሕዳሴው ግድብ ግንባታ ከ179 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ

Mar 15, 2025

IDOPRESS

ዲላ፤መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴው ግድብ ግንባታ ከ179 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ የሕዳሴው ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ገለጸ።


በክልሉ በቀጣይ ህዝባዊ ተሳትፎን በማጠናከር ገቢን ለማሳደግ በየደረጃው የንቅናቄ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑም ተመላክቷል።


የጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ዘርፉ አጥናፉ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የክልሉ ህዝብ ለሕዳሴው ግድብ የቦንድ ግዥ በመፈጸም ድጋፉን እያጠናከረና አሻራውን እያሳረፈ ይገኛል ።


በተለይ የሕዳሴው ግድብ ዋንጫ ወደ ክልሉ መምጣትን ተከትሎ በተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች ዋንጫውን በማዘዋወር የገቢ ማሰባሰብ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።


በዚህም በተያዘው ዓመት ያለፉት ስድስት ወራት በቦንድ ግዥና በስጦታ ከ179 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።


በክልሉ ዘንድሮ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ ነው" ያሉት ሃላፊው በቀጣይ ወራት የህብረተሰቡን ተሳትፎ በማጠናከር ዕቅዱን ለማሳካት በየደረጃው የንቅናቄ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።


ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአንድነታችን ማሳያና የዛሬው ትውልዱ አድዋ ነው ያሉት አቶ ዘርፉ፣ ህብረተሰቡ በቦንድ ግዥና በተለያየ መንገድ ሲያደርገው የነበረውን ድጋፍ እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026