የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በጎንደር ከተማ በ60 ሚሊዮን ብር የ10 ሼዶች ግንባታ ሥራ እየተከናወነ ነው - አስተዳደሩ

Mar 15, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- በጎንደር ከተማ በዘመናዊ የዶሮ እርባታ ሥራ ለሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞች በ60 ሚሊዮን ብር የ10 ሼዶች ግንባታ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ገለጸ።

የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በከተማው እየተከናወኑ ያሉ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝት ወቅት የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው እንደገለጹት፣ ከተማ አስተዳደሩ በመደበው 60 ሚሊዮን ብር የ10 ሼዶች ግንባታ ሥራ እየተከናወነ ነው።


ሼዶቹ በከተማው በዘመናዊ የዶሮ እርባታ ሥራ ለሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የሚተላለፉ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

በክላስተር በተደራጀ አግባብ በሚከናወነው የዶሮ እርባታ ሥራም አካል ጉዳተኞች በልዩ ሁኔታ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አመልክተዋል።

ከፍተኛ አመራሩ ከሌማት ትሩፋት እንቅስቃሴ በተጨማሪ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በክረምቱ ወራት የሚተከሉ ችግኞች ዝግጅትንም የጎበኘ ሲሆን የከተማውን የኮሪደር ልማት የሥራ እንቅስቃሴን እንደሚመለከትም ታውቋል።


ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን የፍራፍሬ ችግኞች የማፍላትና በንብ ማነብ ሥራ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትም የጉብኝቱ አካል ናቸው።

በጉብኝቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ ድረስ ሳህሉ(ዶ/ር)፣ የርዕሰ መስተዳድሩ የመሠረተ ልማት አማካሪ አቶ ደሴ አሰሜ እንዲሁም የክልሉ መንገዶች ቢሮ ሃላፊ ጋሻው አወቀ(ዶ/ር) ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026