
ጎንደር፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- በጎንደር ከተማ በዘመናዊ የዶሮ እርባታ ሥራ ለሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞች በ60 ሚሊዮን ብር የ10 ሼዶች ግንባታ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ገለጸ።
የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በከተማው እየተከናወኑ ያሉ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።
በጉብኝት ወቅት የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው እንደገለጹት፣ ከተማ አስተዳደሩ በመደበው 60 ሚሊዮን ብር የ10 ሼዶች ግንባታ ሥራ እየተከናወነ ነው።

ሼዶቹ በከተማው በዘመናዊ የዶሮ እርባታ ሥራ ለሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የሚተላለፉ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
በክላስተር በተደራጀ አግባብ በሚከናወነው የዶሮ እርባታ ሥራም አካል ጉዳተኞች በልዩ ሁኔታ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አመልክተዋል።
ከፍተኛ አመራሩ ከሌማት ትሩፋት እንቅስቃሴ በተጨማሪ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በክረምቱ ወራት የሚተከሉ ችግኞች ዝግጅትንም የጎበኘ ሲሆን የከተማውን የኮሪደር ልማት የሥራ እንቅስቃሴን እንደሚመለከትም ታውቋል።

ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን የፍራፍሬ ችግኞች የማፍላትና በንብ ማነብ ሥራ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትም የጉብኝቱ አካል ናቸው።
በጉብኝቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ ድረስ ሳህሉ(ዶ/ር)፣ የርዕሰ መስተዳድሩ የመሠረተ ልማት አማካሪ አቶ ደሴ አሰሜ እንዲሁም የክልሉ መንገዶች ቢሮ ሃላፊ ጋሻው አወቀ(ዶ/ር) ተገኝተዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026