
ጎንደር፤ መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፡- በጎንደር ከተማ በዘመናዊ የዶሮ እርባታ ሥራ ለሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞች በ60 ሚሊዮን ብር የ10 ሼዶች ግንባታ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ገለጸ።
የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በከተማው እየተከናወኑ ያሉ የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።
በጉብኝት ወቅት የከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው እንደገለጹት፣ ከተማ አስተዳደሩ በመደበው 60 ሚሊዮን ብር የ10 ሼዶች ግንባታ ሥራ እየተከናወነ ነው።

ሼዶቹ በከተማው በዘመናዊ የዶሮ እርባታ ሥራ ለሚሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የሚተላለፉ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
በክላስተር በተደራጀ አግባብ በሚከናወነው የዶሮ እርባታ ሥራም አካል ጉዳተኞች በልዩ ሁኔታ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አመልክተዋል።
ከፍተኛ አመራሩ ከሌማት ትሩፋት እንቅስቃሴ በተጨማሪ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በክረምቱ ወራት የሚተከሉ ችግኞች ዝግጅትንም የጎበኘ ሲሆን የከተማውን የኮሪደር ልማት የሥራ እንቅስቃሴን እንደሚመለከትም ታውቋል።

ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን የፍራፍሬ ችግኞች የማፍላትና በንብ ማነብ ሥራ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትም የጉብኝቱ አካል ናቸው።
በጉብኝቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ ድረስ ሳህሉ(ዶ/ር)፣ የርዕሰ መስተዳድሩ የመሠረተ ልማት አማካሪ አቶ ደሴ አሰሜ እንዲሁም የክልሉ መንገዶች ቢሮ ሃላፊ ጋሻው አወቀ(ዶ/ር) ተገኝተዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025