የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎትን የበለጠ ለማሳለጥ የግል ዘርፉ ተሳትፎ ሊጎለብት ይገባል-ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)

Mar 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 6/2017(ኢዜአ)፦ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎትን የበለጠ ለማሳለጥ የግል ዘርፉ ተሳትፎ ሊጎለብት እንደሚገባ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትሩ ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ።

በወጪ ንግዱ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ላይ ያሉ ዕድሎችና ተግዳሮቶችን በተመለከተ ከዘርፉ ተዋንያን ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ውይይት ተካሂዷል።


በውይይቱ የተሳተፉት አምራቾችና ላኪዎች ምርቶቻቸውን በጥራትና በብዛት ወደ ውጪ ለመላክ የመሰረተ ልማትና ያልተሳለጠ ሎጂስቲክስ አገልግሎት ክፍተት ፈጥሮብናል ብለዋል።

በተለይም ከጅቡቲ ወደብ ጋር ተያይዞ ያለው መጨናነቅና የመንገዱ ብልሽት ለተጨማሪ ወጪና እንግልት የዳረጋቸው መሆኑንም ነው ያነሱት።

መንግስት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡርን ጨምሮ የዘርፉን ተግዳሮቶች ለመፍታት የጀመራቸውን የሪፎርም ስራዎች ያደነቁት ተሳታፊዎቹ፤ ይሁን እንጂ አሁንም የዕቃ ሰነድ አያያዝ፣ ከኮንቴነር እጥረትና ከቀልጣፋ አገልግሎት ጋር ተያይዞ ያልተፈቱ ተግዳሮቶች አሉ ብለዋል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትሩ ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በበኩላቸው መንግስት ባለፉት ጥቂት ዓመታት በዘርፉ የነበሩ ተግዳሮቶችን ለመፍታት በወሰዳቸው እርምጃዎች የወጪ ንግዱ ላይ መሻሻል መኖሩን አንስተዋል።

ሆኖም የወጪና ገቢ ምርቶች ሚዛን አለመመጣጠንን ጨምሮ በሎጂስቲክስ አቅርቦት ላይ ክፍተቶች መኖራቸውን አመልክተዋል።

ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስን ማቀላጠፍ ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግና የንግድ ሚዛኑን ለመጠበቅ ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።

ለዚህም የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር አክሲዮን ማህበር የመልቲሞዳል ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ጠቅሰው፤ ይህም የወጪ ንግድን ለማሳደግ የጎላ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

ከኢትዮ-ጅቡቲ መንገድ መሰረተ ልማት ጋር ተያይዞ ይቀርብ የነበረውን ተደጋጋሚ የመንገድ ጥገና ጥያቄ ለመመለስም ከጅቡቲ መንግስት ጋር በቅርበት እየተሰራ ነው ብለዋል።

የወጪ ንግዱን ወጪ ቆጣቢና ቀልጣፋ በሆነ ሎጂስቲክስ ለማሳለጥ መንግስት ከሚያከናውናቸው ተግባራት ባለፈ የግል ዘርፉ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑንም ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር አክሲዮን ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ታከለ ኡማ በበኩላቸው፤ የባቡር አገልግሎቱን ፈጣን፣ ቀልጣፋና ወጪ ቆጣቢ በማድረግ የወጪ ንግዱ እንዲሳለጥ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ተቋማቸው የወጪ ንግዱን ለማቀላጠፍ ከመሰረተ ልማት ጀምሮ ፈጣን አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ አሰራሮች መዘርጋቱንም ተናግረዋል።

የባቡር ትራንስፖርት ቡና፣ የቁም እንሰሳት፣ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ ለወጪ ንግድ ምርቶች ምቹና አስተማማኝ በመሆኑ ላኪዎች ከድርጅቱ ጋር እንዲሰሩ ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026