የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የፈጠራ ውጤቶቻችን ተኪ ምርቶችን በማምረት የውጭ ምንዛሬን ለማዳን የሚያግዙ ናቸው

Mar 18, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፦የፈጠራና የምርምር ውጤቶቻችን ተኪ ምርቶችን በማምረት የውጭ ምንዛሬን ለማዳን የሚያግዙ ናቸው ሲሉ በትግራይ ክልል የአዕምሯዊ ንብረት የባለቤትነት ሰርተፊኬት የተሰጣቸው የፈጠራ ባለቤቶች ገለጹ።


በትግራይ ክልል በበጀት ዓመቱ ስምንት ወራት 55 ለሚሆኑ የፈጠራና የምርምር ውጤቶች የአዕምሯዊ ንብረት የባለቤትነት እውቅናና ማረጋገጫ ሰርተፊኬት መሰጠቱም ተገልጿል።


በትግራይ ክልል የአዕምሯዊ ንብረት የባለቤትነት ሰርተፊኬት የተሰጣቸው የፈጠራ ባለቤቶች፤የፈጠራና የምርምር ውጤቶቻቸው ተኪ ምርቶችን በማምረት የውጭ ምንዛሬን ለማዳን የሚያግዙ መሆናቸውን ገልጸዋል።


የፈጠራና የምርምር ውጤቶቹን ወደ ተግባር በመቀየር የስራ ዕድል ለመፍጠር በማቀድ እየተንቀሳቀሱ መሆኑንም ተናግረዋል።


ከሰባት የምርምር ዓመታት በኋላ እውቅና እንደተሰጣቸው የገለፁት የኮምፖስት (የተፈጥሮ ማዳበሪያ) ተማራማሪው ካህሳይ ሃይለ ኪሮስ (ዶ/ር)፤ ደረቅ ቆሻሻና አረምን አብላልቶ ወደ ኮምፖስት የሚቀይር የፈጠራ ስራ ማፍለቃቸውን ገልፀዋል።


የግብርና ልማትን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግም ከባለሃብት ጋር በሽርክና ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የኮምፖስት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ በአዲስ አበባ ቃሊቲ አካባቢ እያቋቋሙ መሆኑን አስረድተዋል።


በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በኤሌክትሪካል እና ኮምፒዩተር ኢንጂነሪንግ እንደተመረቀች የገለፀችው ወጣቷ ተማራማሪ ሜሪን ወልደ ስላሴ፤ ከፈጠራ ውጤቶቿ ምርቶች መካከል የመሬት ወለል ንጣፍ፣ግድግዳ ላይ የሚሰቀሉ ጌጦች፣ለምግብና መጠጥ የሚያገለግሉ ዕቃዎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ጌጣጌጦችን ለአብነት ጠቅሳለች።


በቀጣይ ዓመት ያላትን ዕውቀት ለሌሎች ለማካፈል የስልጠና ማዕከል ለመክፈት እቅድ እንዳላት ገልፃለች።


የበለስ ተክልን በማጥፋት ላይ የሚገኝ ''ኮችንያል'' የተባለ ተባይን የሚያጠፋ ፈሳሽ መድኃኒት በምርምር በማግኘት የአዕምሮአዊ ንብረት ማረጋገጫ ባለቤትነት ሰርተፊኬት እንደተሰጣቸው የገለፁት ደግሞ አቶ ጎይቶም ገብረፃድቅ ናቸው።


በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የኢኖቬሽን ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ የአዕምሯዊ ንብረት ምዝገባ ዳሬክተር አቶ ገብረፃድቅ ተስፋይ፤በበጀት ዓመቱ ስምንት ወራት ለቢሮው ከቀረቡ 59 የምርምርና ፈጠራ ውጤቶች መካከል ለ55ቱ የባለቤትነት ማረጋገጫ እውቅና ተሰጥቷል ብለዋል።


የምርምር እና የፈጠራ ውጤቶቹም ችግር ፈቺ ስለመሆናቸው በሙከራ ፍተሻ የተደረገባቸው እንደሆኑም ተናግረዋል።


በተጨማሪም የምርምር ውጤቶቹ በውጭ ምንዛሪ የሚገዙ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካትና ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት እንደሚያስችሉ የታመነባቸው ናቸው ብለዋል።


የፈጠራ እና ምርምር ሥራዎቹ በግብርና፣በማኑፋክቸሪንግ፣ በኮንስትራክሽን፣በአግሮ ፕሮሰሲንግ፣በጤና እና ሌሎች ዘርፎች ላይ ያተኮሩ መሆናቸውንም ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025