አዲስ አበባ፤መጋቢት 8/2017 (ኢዜአ ):-"ኢንቨስት ኢትዮጵያ 2025" ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ፎረም ግንቦት 4 እና 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይደረጋል።
የኢንቨስትመንት ፎረሙ በመንግስት ተቋማት፣የግሉ ዘርፍ እና የልማት አጋሮች የጋራ ትብብር የሚካሄድ ነው።
በፎረሙ ላይ ከዓለም ዙሪያ የተወጣጡ ከአንድ ሺህ በላይ ሰዎች ይታደሙበታል ተብሎ ይጠበቃል።
ዓለም አቀፍ ሁነቱን ለማዘጋጀት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ስራ ተጀምሯል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው፥ ፎረሙ የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት አማራጭ ማስተዋወቅ እና የኢኮኖሚ እድገትን ማሳለጥ ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልጸዋል።
የተለያዩ ባለድርሻ አካላት እየተለወጠ በመጣው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ስነ ምህዳር ዙሪያ እንደሚወያዩ አመልክተዋል።
የግሉ ዘርፍ በኢትዮጵያ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዘርፍ ውስጥ ያለውን ተሳትፎ ማሳደግ ተያይዞም የመንግስት እና የግል አጋርነት ማጎልበት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚካሄድ ጠቁመዋል።
በፎረሙ ላይ ባለሃብቶች፣የፋይናንስ ተቋማት፣የልማት አጋሮች፣ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እንደሚሳተፉ ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025