የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

“ኢንቨስት ኢትዮጵያ” ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመት ፎረም በግንቦት ወር ይካሄዳል

Mar 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 8/2017 (ኢዜአ ):-"ኢንቨስት ኢትዮጵያ 2025" ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ፎረም ግንቦት 4 እና 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይደረጋል።


የኢንቨስትመንት ፎረሙ በመንግስት ተቋማት፣የግሉ ዘርፍ እና የልማት አጋሮች የጋራ ትብብር የሚካሄድ ነው።


በፎረሙ ላይ ከዓለም ዙሪያ የተወጣጡ ከአንድ ሺህ በላይ ሰዎች ይታደሙበታል ተብሎ ይጠበቃል።


ዓለም አቀፍ ሁነቱን ለማዘጋጀት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ስራ ተጀምሯል።


የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው፥ ፎረሙ የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት አማራጭ ማስተዋወቅ እና የኢኮኖሚ እድገትን ማሳለጥ ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልጸዋል።


የተለያዩ ባለድርሻ አካላት እየተለወጠ በመጣው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ስነ ምህዳር ዙሪያ እንደሚወያዩ አመልክተዋል።


የግሉ ዘርፍ በኢትዮጵያ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዘርፍ ውስጥ ያለውን ተሳትፎ ማሳደግ ተያይዞም የመንግስት እና የግል አጋርነት ማጎልበት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚካሄድ ጠቁመዋል።


በፎረሙ ላይ ባለሃብቶች፣የፋይናንስ ተቋማት፣የልማት አጋሮች፣ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እንደሚሳተፉ ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.