
አዲስ አበባ፤መጋቢት 8/2017 (ኢዜአ ):-"ኢንቨስት ኢትዮጵያ 2025" ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ፎረም ግንቦት 4 እና 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይደረጋል።
የኢንቨስትመንት ፎረሙ በመንግስት ተቋማት፣የግሉ ዘርፍ እና የልማት አጋሮች የጋራ ትብብር የሚካሄድ ነው።
በፎረሙ ላይ ከዓለም ዙሪያ የተወጣጡ ከአንድ ሺህ በላይ ሰዎች ይታደሙበታል ተብሎ ይጠበቃል።
ዓለም አቀፍ ሁነቱን ለማዘጋጀት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ስራ ተጀምሯል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው፥ ፎረሙ የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት አማራጭ ማስተዋወቅ እና የኢኮኖሚ እድገትን ማሳለጥ ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልጸዋል።
የተለያዩ ባለድርሻ አካላት እየተለወጠ በመጣው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ስነ ምህዳር ዙሪያ እንደሚወያዩ አመልክተዋል።
የግሉ ዘርፍ በኢትዮጵያ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዘርፍ ውስጥ ያለውን ተሳትፎ ማሳደግ ተያይዞም የመንግስት እና የግል አጋርነት ማጎልበት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር እንደሚካሄድ ጠቁመዋል።
በፎረሙ ላይ ባለሃብቶች፣የፋይናንስ ተቋማት፣የልማት አጋሮች፣ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እንደሚሳተፉ ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025