የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ከአውሮፓ ህብረት ተወካዮች ጋር ተወያዩ

Mar 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፦ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ከአውሮፓ ህብረት ተወካዮች ጋር ተወያይተዋል።

በዓለም ንግድ ድርጅት የኢትዮጵያ የተደራዳሪ ቡድን በ5ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት የስራ ላይ ቡድን ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ይገኛል።

ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንደገለጹት ተደራዳሪ ቡድኑ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ከአውሮፓ ህብረት ተወካዮች ጋር የሁለትዮሽ የገበያ እድል ድርድርን የተመለከተ ስብሰባ አድርጓል።


የአውሮፓ ህብረት ላቀረባቸው ጥያቄዎች ከሃገራችን ዘላቂ ጥቅም አንጻር የተቃኙ ምላሾችን ሰተናል ብለዋል፡፡

በመጪው ረቡዕ ከሚካሄድው የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ስብሰባ ጎን ለጎን ከተለያዩ ሀገራት ተወካዮች ጋር የሁለትዮሽ ስብሰባዎች እንደሚደረጉም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.