
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዓለም ንብ ቀንና የዓለም አቀፍ የምግብ ስርዓት ሽግግር አውደ ጥናትን ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት እያደረገች እንደምትገኝ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) ረዳት ዋና ዳይሬክተርና የአፍሪካ ቀጣናዊ ተወካይ አበበ ኃይለ ገብርኤል እና ከድርጅቱ የኢትዮጵያ ተወካይ ፋራይ ዚሙድዚን ጋር በፅህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።
ሁለቱ ወገኖች በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
ኢትዮጵያ ዘንድሮ በምታስተናግደው ሁለተኛውን የዓለም የንብ ቀንና ዓለም አቀፍ የምግብ ስርዓት ሽግግር አውደ ጥናት እንዲሁም የግብርናውን ዘርፍ ለማሳደግ እየተሰሩ ባሉ ኢኒሼቲቮች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡
የዓለም የንብ ቀንና ዓለም አቀፍ የምግብ ስርዓት ሽግግር አውደ ጥናትን ለማካሄድ ኮሚቴዎች ተዋቅረው ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ በውይይቱ ወቅት ተገልጿል፡፡
የዓለም የንብ ቀን ዘንድሮ ከግንቦት 12 እስከ 14 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲሁም ዓለም አቀፍ የምግብ ስርዓት ሽግግር አውደ ጥናት ደግሞ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ይካሄዳሉ፡፡
በሁለቱ ዝግጅቶች እና የግብርናውን ዘርፍ ለማሳደግ እየተሰሩ ባሉ ኢንሼቲቮች ላይ ውይይት በማድረግ የጋራ መግባባት ላይ መደረሱን ከግብርና ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025