የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ሁነቶቹን ለማስተናገድ ዝግጅት እያደረገች ነው

Mar 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዓለም ንብ ቀንና የዓለም አቀፍ የምግብ ስርዓት ሽግግር አውደ ጥናትን ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት እያደረገች እንደምትገኝ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ።

ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) ረዳት ዋና ዳይሬክተርና የአፍሪካ ቀጣናዊ ተወካይ አበበ ኃይለ ገብርኤል እና ከድርጅቱ የኢትዮጵያ ተወካይ ፋራይ ዚሙድዚን ጋር በፅህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።

ሁለቱ ወገኖች በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል።

ኢትዮጵያ ዘንድሮ በምታስተናግደው ሁለተኛውን የዓለም የንብ ቀንና ዓለም አቀፍ የምግብ ስርዓት ሽግግር አውደ ጥናት እንዲሁም የግብርናውን ዘርፍ ለማሳደግ እየተሰሩ ባሉ ኢኒሼቲቮች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡

የዓለም የንብ ቀንና ዓለም አቀፍ የምግብ ስርዓት ሽግግር አውደ ጥናትን ለማካሄድ ኮሚቴዎች ተዋቅረው ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ በውይይቱ ወቅት ተገልጿል፡፡

የዓለም የንብ ቀን ዘንድሮ ከግንቦት 12 እስከ 14 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲሁም ዓለም አቀፍ የምግብ ስርዓት ሽግግር አውደ ጥናት ደግሞ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ይካሄዳሉ፡፡

በሁለቱ ዝግጅቶች እና የግብርናውን ዘርፍ ለማሳደግ እየተሰሩ ባሉ ኢንሼቲቮች ላይ ውይይት በማድረግ የጋራ መግባባት ላይ መደረሱን ከግብርና ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026