
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዓለም ንብ ቀንና የዓለም አቀፍ የምግብ ስርዓት ሽግግር አውደ ጥናትን ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት እያደረገች እንደምትገኝ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) ረዳት ዋና ዳይሬክተርና የአፍሪካ ቀጣናዊ ተወካይ አበበ ኃይለ ገብርኤል እና ከድርጅቱ የኢትዮጵያ ተወካይ ፋራይ ዚሙድዚን ጋር በፅህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።
ሁለቱ ወገኖች በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
ኢትዮጵያ ዘንድሮ በምታስተናግደው ሁለተኛውን የዓለም የንብ ቀንና ዓለም አቀፍ የምግብ ስርዓት ሽግግር አውደ ጥናት እንዲሁም የግብርናውን ዘርፍ ለማሳደግ እየተሰሩ ባሉ ኢኒሼቲቮች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡
የዓለም የንብ ቀንና ዓለም አቀፍ የምግብ ስርዓት ሽግግር አውደ ጥናትን ለማካሄድ ኮሚቴዎች ተዋቅረው ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ በውይይቱ ወቅት ተገልጿል፡፡
የዓለም የንብ ቀን ዘንድሮ ከግንቦት 12 እስከ 14 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲሁም ዓለም አቀፍ የምግብ ስርዓት ሽግግር አውደ ጥናት ደግሞ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ይካሄዳሉ፡፡
በሁለቱ ዝግጅቶች እና የግብርናውን ዘርፍ ለማሳደግ እየተሰሩ ባሉ ኢንሼቲቮች ላይ ውይይት በማድረግ የጋራ መግባባት ላይ መደረሱን ከግብርና ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026