
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ)፦ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ ሲካሔድ የቆየው 5ኛው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት የሥራ ቡድን ስብሰባ ተጠናቋል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው 5ኛው የሀገራችን የአለም ንግድ ድርጅት የስራ ቡድን ስብሰባ በስኬት ተጠናቋል ሲሉ አስፍረዋል።
በተለያዩ የድርድር ነጥቦች ዙሪያ ከ110 በላይ ጥያቄዎችን በመቀበል ውጤታማ ድርድር ያካሄደው የድርድር ቡድናችን ማምሻውን ድርድሩን አጠናቅቋል ሲሉም ገልጸዋል።

የሚቀጥለው ስድስተኛው የሥራ ቡድን ስብሰባም በያዝነው ዓመት ሐምሌ ወር ላይ እንዲካሄድ ከስምምነት ደርሰናል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ በ2018 ካሜሩን ላይ በሚካሄደው 14ኛው የዓለም ንግድ ሚኒስትሮች ስብሰባ፤ የዓለም ንግድ ቤተሰብን እንድትቀላቀል ሁላችንም የራሳችንን የቤት ሥራ ለመሥራት ተስማምተን ድርድራችንን ቋጭተናል ብለዋል።
በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናትም ቀሪ የሁለትዮሽ ድርድሮችን ጨምሮ ከጽሕፈት ቤቱ ጋር የሚደረጉ ውይይቶች እንደሚኖሩም ገልጸዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026