አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ)፦ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ ሲካሔድ የቆየው 5ኛው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት የሥራ ቡድን ስብሰባ ተጠናቋል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው 5ኛው የሀገራችን የአለም ንግድ ድርጅት የስራ ቡድን ስብሰባ በስኬት ተጠናቋል ሲሉ አስፍረዋል።
በተለያዩ የድርድር ነጥቦች ዙሪያ ከ110 በላይ ጥያቄዎችን በመቀበል ውጤታማ ድርድር ያካሄደው የድርድር ቡድናችን ማምሻውን ድርድሩን አጠናቅቋል ሲሉም ገልጸዋል።
የሚቀጥለው ስድስተኛው የሥራ ቡድን ስብሰባም በያዝነው ዓመት ሐምሌ ወር ላይ እንዲካሄድ ከስምምነት ደርሰናል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ በ2018 ካሜሩን ላይ በሚካሄደው 14ኛው የዓለም ንግድ ሚኒስትሮች ስብሰባ፤ የዓለም ንግድ ቤተሰብን እንድትቀላቀል ሁላችንም የራሳችንን የቤት ሥራ ለመሥራት ተስማምተን ድርድራችንን ቋጭተናል ብለዋል።
በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናትም ቀሪ የሁለትዮሽ ድርድሮችን ጨምሮ ከጽሕፈት ቤቱ ጋር የሚደረጉ ውይይቶች እንደሚኖሩም ገልጸዋል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025