
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ)፦ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ ሲካሔድ የቆየው 5ኛው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት የሥራ ቡድን ስብሰባ ተጠናቋል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው 5ኛው የሀገራችን የአለም ንግድ ድርጅት የስራ ቡድን ስብሰባ በስኬት ተጠናቋል ሲሉ አስፍረዋል።
በተለያዩ የድርድር ነጥቦች ዙሪያ ከ110 በላይ ጥያቄዎችን በመቀበል ውጤታማ ድርድር ያካሄደው የድርድር ቡድናችን ማምሻውን ድርድሩን አጠናቅቋል ሲሉም ገልጸዋል።

የሚቀጥለው ስድስተኛው የሥራ ቡድን ስብሰባም በያዝነው ዓመት ሐምሌ ወር ላይ እንዲካሄድ ከስምምነት ደርሰናል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ በ2018 ካሜሩን ላይ በሚካሄደው 14ኛው የዓለም ንግድ ሚኒስትሮች ስብሰባ፤ የዓለም ንግድ ቤተሰብን እንድትቀላቀል ሁላችንም የራሳችንን የቤት ሥራ ለመሥራት ተስማምተን ድርድራችንን ቋጭተናል ብለዋል።
በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናትም ቀሪ የሁለትዮሽ ድርድሮችን ጨምሮ ከጽሕፈት ቤቱ ጋር የሚደረጉ ውይይቶች እንደሚኖሩም ገልጸዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026