የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ፕሬዝዳንት ፑቲን የሩሲያ ኩባንያዎች በብሪክስ ፕሮጀክቶች ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ጠየቁ

Mar 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ):- የሩሲያ ኩባንያዎች በብሪክስ የጋራ ፕሮጀክቶች ላይ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጥሪ አቅርበዋል።

ፑቲን በሩሲያ የኢንዱስትዎች እና የስራ ፈጣሪዎች ህብረት ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር የሩሲያ የንግድ ማህበረሰብ በብሪክስ ፕሮጀክቶች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

ቭላድሚር ፑቲን የቢብሪክስ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2024 የ4 ነጥብ 9 በመቶ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገባቸውን አውስተዋል።

በተለያዩ የዓለም ክፍሎች በቀጣይ አስርት ዓመታት የሚኖረው የዕድገት መጠን የተረጋጋ ሆኖ እንደሚቀጥል ግምታቸውን አስቀምጠዋል።

የሩሲያ የንግድ ማህበረሰብ ከብሪክስ አባል ሀገራት አጋሮች እና ቀጣይ አባል ከሚሆኑ ሀገራት ጋር የጋራ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ የተሻለ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

ሩሲያ ከብሪክስ አጋሮች ጋር በኢነርጂ፣ ኢንዱስትሪ፣ ፋይናንስ እና ሌሎች ዘርፎች በትብብር እየሰራች እንደምትገኝ የብሪክስ ቲቪ ዘገባ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.