የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ባለፉት ስምንት ወራት ከ3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሮላቸዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Mar 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017(ኢዜአ)፡- ባለፉት ስምንት ወራት ከ3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በፌዴራል መንግስት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የአፈፃፀም ሪፖርትን መነሻ በማድረግ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ እና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።

በማብራሪያቸውም መንግሥት ባለፉት ስምንት ወራት በትኩረት ከሰራባቸው ዘርፎች አንዱ የስራ ዕድል ፈጠራ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም በሀገር ውስጥ ወደ 2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዜጎች የስራ ድል እንደተፈጠረላቸው ገልጸዋል።

በውጭ ሀገር የስራ ስምሪትም ከ300 ሺህ በላይ ዜጎች ስራ ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል።

እንዲሁም በርቀት የሥራ ዕድል አማካይነት ከ45 ሺህ በላይ ያላነሱ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ሆነው ለውጭ ሀገር ኩባንያዎች እየሰሩ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።

በድምሩ ከ3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የስራ እድል ማግኘታቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት።

በከተማ እና በገጠር የኮሪደር ስራዎች እና ልዩ ልዩ ኢኒሼቲቮች ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል መፈጠሩንም ነው የገለጹት።

በቀጣይም የሥራ ዕድል ፈጠራን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚያስፈልግ በማመላከት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.