
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017(ኢዜአ)፡- ባለፉት ስምንት ወራት ከ3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በፌዴራል መንግስት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የአፈፃፀም ሪፖርትን መነሻ በማድረግ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ እና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።
በማብራሪያቸውም መንግሥት ባለፉት ስምንት ወራት በትኩረት ከሰራባቸው ዘርፎች አንዱ የስራ ዕድል ፈጠራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በሀገር ውስጥ ወደ 2 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዜጎች የስራ ድል እንደተፈጠረላቸው ገልጸዋል።
በውጭ ሀገር የስራ ስምሪትም ከ300 ሺህ በላይ ዜጎች ስራ ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል።
እንዲሁም በርቀት የሥራ ዕድል አማካይነት ከ45 ሺህ በላይ ያላነሱ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ሆነው ለውጭ ሀገር ኩባንያዎች እየሰሩ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።
በድምሩ ከ3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የስራ እድል ማግኘታቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት።
በከተማ እና በገጠር የኮሪደር ስራዎች እና ልዩ ልዩ ኢኒሼቲቮች ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል መፈጠሩንም ነው የገለጹት።
በቀጣይም የሥራ ዕድል ፈጠራን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚያስፈልግ በማመላከት።
አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የ...
Jun 16, 2026
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026