የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኮሚሽኑ ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን አቅም ፈጥሯል

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 24/2017 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ኮሚሽን ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሪፎርም ስራዎችን በማከናወን ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን አቅም መፍጠሩን የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቀበታ ገለጹ።


"ትናንት፣ዛሬና ነገ ለኢትጵያ ልዕልና "በሚል መሪ ሃሳብ ባለፉት የለውጥ ዓመታት እንደ ሀገር በተገኙ ስኬቶችና በቀጣይ የቤት ስራዎች ዙሪያ የጉምሩክ ኮሚሽን አመራርና ሰራተኞች ምክክር አድርገዋል።


የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቀበታ፥ ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት በፖለቲካዊ ፤በኢኮኖሚ፣ በተቋማት የሪፎርም ስራዎች እና በዲፕሎማሲ እንቅስቃሴዎች ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡


በአገሪቱ ለጉምሪክ አሰራር ማነቆ የነበሩ ህጎችን በማሻሻል አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር እንዲጣጣሙ ምቹ መደላድል መፈጠሩንም ገልጸዋል።


የጉምሩክ ኮሚሽን ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት የአሰራር ስርአቱን ለማዘመን በርካታ የሪፎርም ስራዎችን ማከናወኑን አስታውሰው፥ ይህም ኮሚሽኑ ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን አቅም እንደፈጠረለት ጠቅሰዋል።


ከለውጡ በፊት ኮሚሽኑ በተለያዩ እቃዎች ላይ ተገቢውን ዋጋ በመተመን ተገቢውን ቀረጥና ታክስ ከመሰብሰብ አኳያ ክፍተት ይታይበት እንደነበር ተናግረዋል።


ባለፉት የለውጥ ዓመታት ኮሚሽኑ አሰራሮቹን በቴክኖሎጂ ማስደገፍ በመቻሉ ተገቢውን አገልግሎት በመስጠት ገቢ የመሰብሰብ አቅሙን ማሳደግ መቻሉን አስታውቀዋል፡፡


ኮሚሽኑ በራስ አቅም ቴክኖሎጂዎችን በማበልጸግ ሀገሪቱ ከውጭ በምታስገባቸው እቃዎች ላይ ተገቢውን ቀረጥና ታክስ መተመን የሚያስችል አቅም መፍጠሩን አስታውቀዋል፡፡


ከዚህም በተጨማሪ ኮሚሽኑ ያደረጋቸው የሪፎርም ማሻሻያዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለተሰማሩ ባለሃብቶች የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋ እንዲሆኑ አስችሏል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.