
አዲስ አበባ፤መጋቢት 24/2017 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ኮሚሽን ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሪፎርም ስራዎችን በማከናወን ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን አቅም መፍጠሩን የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቀበታ ገለጹ።
"ትናንት፣ዛሬና ነገ ለኢትጵያ ልዕልና "በሚል መሪ ሃሳብ ባለፉት የለውጥ ዓመታት እንደ ሀገር በተገኙ ስኬቶችና በቀጣይ የቤት ስራዎች ዙሪያ የጉምሩክ ኮሚሽን አመራርና ሰራተኞች ምክክር አድርገዋል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቀበታ፥ ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት በፖለቲካዊ ፤በኢኮኖሚ፣ በተቋማት የሪፎርም ስራዎች እና በዲፕሎማሲ እንቅስቃሴዎች ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡
በአገሪቱ ለጉምሪክ አሰራር ማነቆ የነበሩ ህጎችን በማሻሻል አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር እንዲጣጣሙ ምቹ መደላድል መፈጠሩንም ገልጸዋል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት የአሰራር ስርአቱን ለማዘመን በርካታ የሪፎርም ስራዎችን ማከናወኑን አስታውሰው፥ ይህም ኮሚሽኑ ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን አቅም እንደፈጠረለት ጠቅሰዋል።
ከለውጡ በፊት ኮሚሽኑ በተለያዩ እቃዎች ላይ ተገቢውን ዋጋ በመተመን ተገቢውን ቀረጥና ታክስ ከመሰብሰብ አኳያ ክፍተት ይታይበት እንደነበር ተናግረዋል።
ባለፉት የለውጥ ዓመታት ኮሚሽኑ አሰራሮቹን በቴክኖሎጂ ማስደገፍ በመቻሉ ተገቢውን አገልግሎት በመስጠት ገቢ የመሰብሰብ አቅሙን ማሳደግ መቻሉን አስታውቀዋል፡፡
ኮሚሽኑ በራስ አቅም ቴክኖሎጂዎችን በማበልጸግ ሀገሪቱ ከውጭ በምታስገባቸው እቃዎች ላይ ተገቢውን ቀረጥና ታክስ መተመን የሚያስችል አቅም መፍጠሩን አስታውቀዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ኮሚሽኑ ያደረጋቸው የሪፎርም ማሻሻያዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለተሰማሩ ባለሃብቶች የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋ እንዲሆኑ አስችሏል ብለዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025