
አዲስ አበባ፤መጋቢት 24/2017 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ኮሚሽን ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሪፎርም ስራዎችን በማከናወን ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን አቅም መፍጠሩን የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቀበታ ገለጹ።
"ትናንት፣ዛሬና ነገ ለኢትጵያ ልዕልና "በሚል መሪ ሃሳብ ባለፉት የለውጥ ዓመታት እንደ ሀገር በተገኙ ስኬቶችና በቀጣይ የቤት ስራዎች ዙሪያ የጉምሩክ ኮሚሽን አመራርና ሰራተኞች ምክክር አድርገዋል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቀበታ፥ ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት በፖለቲካዊ ፤በኢኮኖሚ፣ በተቋማት የሪፎርም ስራዎች እና በዲፕሎማሲ እንቅስቃሴዎች ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡
በአገሪቱ ለጉምሪክ አሰራር ማነቆ የነበሩ ህጎችን በማሻሻል አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር እንዲጣጣሙ ምቹ መደላድል መፈጠሩንም ገልጸዋል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት የአሰራር ስርአቱን ለማዘመን በርካታ የሪፎርም ስራዎችን ማከናወኑን አስታውሰው፥ ይህም ኮሚሽኑ ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን አቅም እንደፈጠረለት ጠቅሰዋል።
ከለውጡ በፊት ኮሚሽኑ በተለያዩ እቃዎች ላይ ተገቢውን ዋጋ በመተመን ተገቢውን ቀረጥና ታክስ ከመሰብሰብ አኳያ ክፍተት ይታይበት እንደነበር ተናግረዋል።
ባለፉት የለውጥ ዓመታት ኮሚሽኑ አሰራሮቹን በቴክኖሎጂ ማስደገፍ በመቻሉ ተገቢውን አገልግሎት በመስጠት ገቢ የመሰብሰብ አቅሙን ማሳደግ መቻሉን አስታውቀዋል፡፡
ኮሚሽኑ በራስ አቅም ቴክኖሎጂዎችን በማበልጸግ ሀገሪቱ ከውጭ በምታስገባቸው እቃዎች ላይ ተገቢውን ቀረጥና ታክስ መተመን የሚያስችል አቅም መፍጠሩን አስታውቀዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ኮሚሽኑ ያደረጋቸው የሪፎርም ማሻሻያዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለተሰማሩ ባለሃብቶች የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋ እንዲሆኑ አስችሏል ብለዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026