
አዲስ አበባ፤መጋቢት 24/2017 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ኮሚሽን ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሪፎርም ስራዎችን በማከናወን ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን አቅም መፍጠሩን የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቀበታ ገለጹ።
"ትናንት፣ዛሬና ነገ ለኢትጵያ ልዕልና "በሚል መሪ ሃሳብ ባለፉት የለውጥ ዓመታት እንደ ሀገር በተገኙ ስኬቶችና በቀጣይ የቤት ስራዎች ዙሪያ የጉምሩክ ኮሚሽን አመራርና ሰራተኞች ምክክር አድርገዋል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቀበታ፥ ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት በፖለቲካዊ ፤በኢኮኖሚ፣ በተቋማት የሪፎርም ስራዎች እና በዲፕሎማሲ እንቅስቃሴዎች ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡
በአገሪቱ ለጉምሪክ አሰራር ማነቆ የነበሩ ህጎችን በማሻሻል አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር እንዲጣጣሙ ምቹ መደላድል መፈጠሩንም ገልጸዋል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት የአሰራር ስርአቱን ለማዘመን በርካታ የሪፎርም ስራዎችን ማከናወኑን አስታውሰው፥ ይህም ኮሚሽኑ ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን አቅም እንደፈጠረለት ጠቅሰዋል።
ከለውጡ በፊት ኮሚሽኑ በተለያዩ እቃዎች ላይ ተገቢውን ዋጋ በመተመን ተገቢውን ቀረጥና ታክስ ከመሰብሰብ አኳያ ክፍተት ይታይበት እንደነበር ተናግረዋል።
ባለፉት የለውጥ ዓመታት ኮሚሽኑ አሰራሮቹን በቴክኖሎጂ ማስደገፍ በመቻሉ ተገቢውን አገልግሎት በመስጠት ገቢ የመሰብሰብ አቅሙን ማሳደግ መቻሉን አስታውቀዋል፡፡
ኮሚሽኑ በራስ አቅም ቴክኖሎጂዎችን በማበልጸግ ሀገሪቱ ከውጭ በምታስገባቸው እቃዎች ላይ ተገቢውን ቀረጥና ታክስ መተመን የሚያስችል አቅም መፍጠሩን አስታውቀዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ኮሚሽኑ ያደረጋቸው የሪፎርም ማሻሻያዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለተሰማሩ ባለሃብቶች የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋ እንዲሆኑ አስችሏል ብለዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026