የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የከተማው ወጣቶች የቴክኖሎጂ እውቀታቸውን በማዳበር  ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ  እንዳለባቸው ተገለጸ

Apr 7, 2025

IDOPRESS

ደብረብርሀን ፤መጋቢት 26/ 2017(ኢዜአ) ፡-የደብረ ብርሃን ወጣቶች የቴክኖሎጂ እውቀታቸውን በማዳበር ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ እንዳለባቸው የከተማው አስተዳደር ገለጸ።

የከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ ሶስት ዓመታት 12 ሺህ ወጣቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማሰልጠን እየሰራ መሆኑም ተመላክቷል።

ከተማ አስተዳደሩ ከኪያሜድ ጤና ሳይንስና ቢዝነስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር "ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለትምህርት ጥራት ውጤታማነት ያለው አስተዋጽኦ" በሚል መሪ ሃሳብ በኮደርስ ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጥቷል።

ምክትል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ እንዳሉት ወጣቶች አዳዲስ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ራሳቸውንና አገራቸውን ሊጠቅሙ ይገባል።


በዚህም የከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ ሶስት ዓመታት 12 ሺህ ወጣቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማሰልጠን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በዚህ ዓመት የመንግስት ሰራተኞችን ጨምሮ ሶስት ሺህ ሰዎችን ለማሰልጠን ታቅዶ እስካሁን ከ1 ሺህ 700 በላይ ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ መደረጉን ተናግረዋል።

የተጀመረውን ስልጠና ለማጠናከርም የኪያሜድ ጤና ሳይንስና ቢዝነስ ኮሌጅ መድረክ በማዘጋጀት ወጣቶችን ለማንቃት እያደረገ ያለው ጥረት የሚመሰገን ነው ብለዋል።


የኪያሜድ ጤና ሳይንስና ቢዝነስ ኮሌጅ ዲን አቶ መርሻ አሰፋ እንዳሉት መድረኩ ተማሪዎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ በማተኮር ራሳቸውን ለማብቃት እንዲችሉ ለማድረግ ነው።

በአርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ ያገኘነው ስልጠና አዳዲስ መተግበሪያዎችን በማበልጸግና በመጠቀም በቴክኖሎጂው ዘርፍ ሀገርን ተወዳዳሪ ለማድረግ የበኩሉን እንደሚወጣ የገለጸው ደግሞ ተማሪ ሲሳይ ማሞ ነው።

ሌላው የስልጠናው ተሳታፊ ተማሪ ኤልያስ አላዩ በበኩሉ የኮደርስ ስልጠናው ለትምህርቱ ውጤታማነት አጋዥ መሆኑን አስረድቷል።

በስልጠናው ላይም የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.