
ደብረብርሀን ፤መጋቢት 26/ 2017(ኢዜአ) ፡-የደብረ ብርሃን ወጣቶች የቴክኖሎጂ እውቀታቸውን በማዳበር ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ እንዳለባቸው የከተማው አስተዳደር ገለጸ።
የከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ ሶስት ዓመታት 12 ሺህ ወጣቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማሰልጠን እየሰራ መሆኑም ተመላክቷል።
ከተማ አስተዳደሩ ከኪያሜድ ጤና ሳይንስና ቢዝነስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር "ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለትምህርት ጥራት ውጤታማነት ያለው አስተዋጽኦ" በሚል መሪ ሃሳብ በኮደርስ ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጥቷል።
ምክትል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ እንዳሉት ወጣቶች አዳዲስ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ራሳቸውንና አገራቸውን ሊጠቅሙ ይገባል።

በዚህም የከተማ አስተዳደሩ በቀጣይ ሶስት ዓመታት 12 ሺህ ወጣቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማሰልጠን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በዚህ ዓመት የመንግስት ሰራተኞችን ጨምሮ ሶስት ሺህ ሰዎችን ለማሰልጠን ታቅዶ እስካሁን ከ1 ሺህ 700 በላይ ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ መደረጉን ተናግረዋል።
የተጀመረውን ስልጠና ለማጠናከርም የኪያሜድ ጤና ሳይንስና ቢዝነስ ኮሌጅ መድረክ በማዘጋጀት ወጣቶችን ለማንቃት እያደረገ ያለው ጥረት የሚመሰገን ነው ብለዋል።

የኪያሜድ ጤና ሳይንስና ቢዝነስ ኮሌጅ ዲን አቶ መርሻ አሰፋ እንዳሉት መድረኩ ተማሪዎች በዲጂታል ቴክኖሎጂ ላይ በማተኮር ራሳቸውን ለማብቃት እንዲችሉ ለማድረግ ነው።
በአርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ ያገኘነው ስልጠና አዳዲስ መተግበሪያዎችን በማበልጸግና በመጠቀም በቴክኖሎጂው ዘርፍ ሀገርን ተወዳዳሪ ለማድረግ የበኩሉን እንደሚወጣ የገለጸው ደግሞ ተማሪ ሲሳይ ማሞ ነው።
ሌላው የስልጠናው ተሳታፊ ተማሪ ኤልያስ አላዩ በበኩሉ የኮደርስ ስልጠናው ለትምህርቱ ውጤታማነት አጋዥ መሆኑን አስረድቷል።
በስልጠናው ላይም የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026