የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተው ተጠቃሚ የሆኑ አርሶ አደሮች

Apr 7, 2025

IDOPRESS

በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተሰማርተው ተጠቃሚ የሆኑ የምስራቅ ሀረርጌ አርሶ አደሮች

አርሶ አደር ዙቤራ አህመድ ይባላሉ። በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ባቢሌ ወረዳ ከ2010 ዓም ጀምሮ በአትክልትና ፍራፍሬ ተሰማርተው ተጠቃሚ መሆናችውን ይገልጻሉ።

በዚህም ፓፓያ፣ ማንጎ፣ ድንች፣ ጥቅል ጎመን እና ሌሎች አትክልትና ፍራፍሬዎችን በስፋት በማምረት ከራሳቸው አልፎ ለገበያ እያቀረቡ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በዚህ ዓመት ከአንድ ሄክታር መሬት ላይ ከደረሰው የፓፓያ ምርት 25 ሺህ ብር ማግኘታቸውን ጠቁመው፤ አሁንም ለመሰብሰብ የደረሰ ምርት መኖሩን ይናገራሉ።

ባስመዘገቡት ውጤትም በክልል ደረጃ ከሁለት ጊዜ በላይ እውቅናና ሽልማት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

በዚህ ስራቸውም መካከለኛ ባለሀብት መሸጋገራቸውን ገልጸው፤ በስራቸው ለ25 ዜጎች ጊዜያዊና ቋሚ የስራ ዕድል መፍጠር መቻላቸውን ተናግረው፤ በቀጣይ የአትክልት ምርትን በማቀነባበር ለተጠቃሚዎች ማድረስ የሚያስችል ግንባታ እያካሄዱ መሆኑን ጠቁመዋል።


በዞኑ የኮምቦልቻ አርሶ አደር ኢብራሂም አሊ በአትክልት ልማት በመሰማራት ጥሩ ውጤት እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል።

የኮምቦልቻ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ ጀማል ጃቢር (ዶ/ር) በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ስራዎች ተከናውነዋል።


በወረዳው በሌማት ትሩፋት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በሌሎች የልማት ስራዎች አመርቂ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸው፤ በመስኖ ልማት ከ7 ሺህ 400 በላይ ሄክታር መሬት በአትክልትና ፍራፍሬ እየለማ መሆኑን ጠቁመዋል።

በኦሮሚያ ክልል የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሚስኪ መሀመድ በበኩላቸው በዞኑ የመሬቱ አቀማመጥ ለእርሻ የማይመች በመሆኑ ያለውን ሃብት በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችል ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።


በዚህም የዞኑ አርሶ አደሮችን በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሰማሩ በማድረግ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚያስችል በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በዚህም እንደየ አካባቢው የአየር ሁኔታ ሙዝና አቮካዶን ጨምሮ በሌሎች የፍራፍሬ ኢኒሼቲቭ እየተተገበረ መሆኑን ጠቁመዋል።

የክልሉ መንግስት ለኢኒሼቲቩ በሰጠው ትኩረት ለዞኑ ለዘር የሚሆኑ የፍራፍሬ ተክል ችግኞችን ለአርሶ አደሮች ተደራሽ በማድረግ እያስፋፋ መሆኑንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025