
አዲስ አበባ፤መጋቢት 28/2017(ኢዜአ):-ኢትዮጵያ እያስመዘገበች ያለው ፈጣን የልማት እንቅስቃሴ መነሳሳት እንደፈጠረባቸው ኢዜአ ያነጋገራቸው የአፍሪካ አገራት ሚኒስትሮች ገለጹ።
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያከናወነቻቸው የልማት ተግባራት የበርካታ አገራትን ቀልብ ስቧል።
ለዚህ አዲስ አበባ የአፍሪካ መዲናና የዓለምአቀፍ ተቋማት መቀመጫነቷን በሚመጥን መልኩ ልማቷ እየተፋጠነ መምጣቱ በዋቢነትም ይጠቅሳሉ።
አዲስ አበባ እያሳየች ያለው ፈጣን ዕድገት የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከልነቷ እንዲጨምር እያደረገም ነው።
ከተማዋ ለዓለምአቀፍና አህጉራዊ ስብሰባዎችን ከመቼውም ጊዜ በላይ ተመራጭ ከመሆን ባለፈ የበርካታ ጎብኝዎችንም ቀልብ እየሳበች ነው።
የፓን አፍሪካ ወጣት አመራሮች ጉባኤ ለመሳተፍ አዲስ አበባ የተገኙት የማሊ፣የጋምቢያና የብሩንዲ የወጣቶች፣ ስፖርትና ባህል ሚኒስትሮች ይህንኑ ነው የሚመሰክሩት።
የማሊ ወጣቶች፣ ስፖርትና ዜግነት ጉዳዮች ሚኒስትር አብዶል ቃሲም በወቅቱ እንደገለጹት፥ ኢትየጵያ ሁሉንም ያሳተፈ የልማት ስራ ማከናወኗ ውጤታማ አድርጓታል።
ብዙሃኑን ያሳተፈ የልማት እንቅስቃሴ ውጤቱ ያማረ እንደሚሆን ከኢትዮጵያ ልምድ መውሰድ እንደሚቻልም ነው ያነሱት።
የጋምቢያ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር ባርይ ባጄ ከአስር ዓመት በፊት በሚያውቋት አዲስ አበባ ፈጣን ለውጥ መደነቃቸውን ይገልጻሉ።
አገራቸውን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ አገራት ከአዲስ አበባ ልማት የዕውቀትና የቴክኖሎጂ ልምድ የመውሰድ ፍላጎት እንዳላቸውም ተናግረዋል።
የቡሩንዲ የምስራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ ጉዳዮች ፤ወጣቶች ስፖርትና ባህል ሚኒስትር ገርቫይስ አምብ አባይሆ፤ የአገራቸውን ወጣቶች ወደ አዲስ አበባ አምጥተው የማስጎብኘት ፍላጎት እንዳላቸው ነው የገለጹት።
በጉባዔው ለመሳተፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ የመጣችው ናሚቢያዊቷ ሻና ግሮዚ አዲስ አበባ በምናብ ከምትታስበው በላይ መሆኗን ገልጻለች።
የኢትዮጵያ ተፈጥሯዊ ውበት ጥበብ በተላበሰ መሰረተ ልማት የበለጠ መጉላቱን በማንሳት።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025