
ሆሳዕና ፤መጋቢት 29/2017 (ኢዜአ)፡- የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን አቅም ለማሳደግ የማኑፋክቸሪንግ ፍኖተ ካርታና የፖሊሲ ማዕቀፍ ተግባራዊ መደረጉን የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ገለጸ።
የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ለማጠናከር ያለመ የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር አለባቸው ንጉሴ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች በሀገር ኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው፡፡

ተቋሙ የማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን ውጤታማ ለማድረግ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት፣ የፋይናንስ፣ የማምረቻና የመሸጫ ቦታን በማቅረብና በማስተዳደር ላይ እየተሰራ ነው፡፡
በአነስተኛና መካከለኛ ደረጃ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞችን የተወዳዳሪነት አቅም ለማሳደግ የማኑፋክቸሪንግ ልማት ፖሊሲ፣ ፍኖተ ካርታና የፖሊሲ ማዕቀፍ ተግባራዊ መደረጉን ተናግረዋል፡፡
በዚህም ባለፉት ሰባት ዓመታት የፋይናንስ ተደራሽነትን ለማሻሻል በተሰራው ስራ 7 ሺህ 525 የአስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን የሊዝ ፋይናንስ ብድር ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል፡፡
ተግባሩን አጠናክሮ በማስቀጠል በዘርፉ የላቀ እመርታ ለማስመዝገብ እንደሚሰራም ነው ዋና ዳይሬክተሩ የገለጹት፡፡
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ በበኩላቸው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጥረት እውን ለማድረግ የአምራች ኢንዱስትሪውን ማስፋፋትና መደገፍ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት ለማምጣት የሀገር ውስጥና የውጪ ባለሀብቶችን በማሳተፍ እየሰራ ነው ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)ን ጨምሮ የክልሉ፣ የዞንና ልዩ ወረዳ አመራሮችና በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶች ተገኝተዋል፡፡
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025