
ሆሳዕና ፤መጋቢት 29/2017 (ኢዜአ)፡- የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን አቅም ለማሳደግ የማኑፋክቸሪንግ ፍኖተ ካርታና የፖሊሲ ማዕቀፍ ተግባራዊ መደረጉን የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ገለጸ።
የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ለማጠናከር ያለመ የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር አለባቸው ንጉሴ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞች በሀገር ኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው፡፡

ተቋሙ የማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን ውጤታማ ለማድረግ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት፣ የፋይናንስ፣ የማምረቻና የመሸጫ ቦታን በማቅረብና በማስተዳደር ላይ እየተሰራ ነው፡፡
በአነስተኛና መካከለኛ ደረጃ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞችን የተወዳዳሪነት አቅም ለማሳደግ የማኑፋክቸሪንግ ልማት ፖሊሲ፣ ፍኖተ ካርታና የፖሊሲ ማዕቀፍ ተግባራዊ መደረጉን ተናግረዋል፡፡
በዚህም ባለፉት ሰባት ዓመታት የፋይናንስ ተደራሽነትን ለማሻሻል በተሰራው ስራ 7 ሺህ 525 የአስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን የሊዝ ፋይናንስ ብድር ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል፡፡
ተግባሩን አጠናክሮ በማስቀጠል በዘርፉ የላቀ እመርታ ለማስመዝገብ እንደሚሰራም ነው ዋና ዳይሬክተሩ የገለጹት፡፡
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ በበኩላቸው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚደረገውን ጥረት እውን ለማድረግ የአምራች ኢንዱስትሪውን ማስፋፋትና መደገፍ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት ለማምጣት የሀገር ውስጥና የውጪ ባለሀብቶችን በማሳተፍ እየሰራ ነው ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)ን ጨምሮ የክልሉ፣ የዞንና ልዩ ወረዳ አመራሮችና በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶች ተገኝተዋል፡፡
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026