
ሚዛን አማን፤ መጋቢት 29/2017(ኢዜአ)፦ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አማራጭ የኃይል አቅርቦትን በመጠቀም ከኤሌክትሪክ መስመር ለራቁ አካባቢዎች ኃይል ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምዕራብ ኦሞ ዞን በ60 ሚሊዮን ብር የተገነባ የጸሐይ ኃይል ፕሮጀክት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ(ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ያልሆኑ ዜጎችን በአማራጭ የኃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ ነው።
በተለይ ከዋናው የኤሌክትሪክ መስመር ርቀው ለሚገኙ ዜጎች የጸሐይ ኃይል አማራጭን በመጠቀም የኤሌክትሪክ አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ለአብነትም በ60 ሚሊዮን ብር ወጪ 5ሺህ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርገው የይርኒ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትም የዚሁ አካል መሆኑን አንስተዋል።
መንግሥት የኃይል አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግ በሰጠው ትኩረት ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት ውስጥ ከ2 ሚሊዮን የሚበልጡ ዜጎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ መላኩ ታዬ ናቸው።
በሌላ በኩል በገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ለ1ሺህ 380 የገጠር ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል ማዳረስ መቻሉንም አክለዋል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገብረማርያም ሰጠኝ በክልሉ ከ200 እስከ 850 ኪሎ ዋት የሚያመነጩ 8 የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
ይህም ከዋና መስመር ርቀው ለሚገኙ ዜጎች የኃይል አማራጭን ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ አቅም እንዳላቸው ተናግረዋል።
የምዕራብ አሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ወንድሙ ቦንባ የጸሐይ ኃይል አማራጭ አገልግሎቱ ለዞኑ ሁለተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ፕሮጀክቱ የዘመናት የሕዝቦችን የኃይል አቅርቦት ጥያቄን የፈታ መሆኑንም አንስተዋል።
ዛሬ በዞኑ መኤኒት ሻሻ ወረዳ የተመረቀው የጸሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት 100 ኪሎ ዋት ኃይል የሚያመነጭ ነው።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026