የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የፈጠራ ውጤቶች የክህሎት ባንክ ተከፈተ

Apr 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ በሰመር ካምፕ እና በክህሎት ኢትዮጵያ መርኃ ግብር የተሰሩ የፈጠራ ውጤቶች የክህሎት ባንክ ተከፍቷል።

የክህሎት ባንኩን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል መርቀው ከፍተውታል።

በክህሎት ባንኩ የሚገኙት የፈጠራ ውጤቶች ባለፈው ዓመት የሰመር ካምፕ ፕሮግራም እንዲሁም በዘንድሮ የክህሎት ኢትዮጵያ ተሳታፊዎች የተሰሩ እና እየተሰሩ ያሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ናቸው።


ይህ በፌዴራል የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የሚገኘው የክህሎት ባንክ የቴክኖሎጂ ባለቤቶችን የፈጠራ ምርቶችን መጠቀምና ማስመረት ከሚፈልጉ ደንበኞች ጋር የሚያገናኝ ነው መሆኑ ተገልጿል።

ባንኩ ለጎብኚዎች ክፍት ሲሆን የመንግስት እና የግል ሴክተሮች የፈጠራ ውጤቶችን በመጎብኘት እንዲመረትላቸው የሚፈልጓቸውን ምርት ትዕዛዝ መስጠት የሚችሉበት ምቹ ሁኔታ መኖሩም ተገልጿል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለ21 ኢንተርፕራይዞች ያዘጋጀው የመስሪያ ቦታ ርክክብ ተደርጓል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.