
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ በሰመር ካምፕ እና በክህሎት ኢትዮጵያ መርኃ ግብር የተሰሩ የፈጠራ ውጤቶች የክህሎት ባንክ ተከፍቷል።
የክህሎት ባንኩን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል መርቀው ከፍተውታል።
በክህሎት ባንኩ የሚገኙት የፈጠራ ውጤቶች ባለፈው ዓመት የሰመር ካምፕ ፕሮግራም እንዲሁም በዘንድሮ የክህሎት ኢትዮጵያ ተሳታፊዎች የተሰሩ እና እየተሰሩ ያሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ናቸው።

ይህ በፌዴራል የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የሚገኘው የክህሎት ባንክ የቴክኖሎጂ ባለቤቶችን የፈጠራ ምርቶችን መጠቀምና ማስመረት ከሚፈልጉ ደንበኞች ጋር የሚያገናኝ ነው መሆኑ ተገልጿል።
ባንኩ ለጎብኚዎች ክፍት ሲሆን የመንግስት እና የግል ሴክተሮች የፈጠራ ውጤቶችን በመጎብኘት እንዲመረትላቸው የሚፈልጓቸውን ምርት ትዕዛዝ መስጠት የሚችሉበት ምቹ ሁኔታ መኖሩም ተገልጿል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለ21 ኢንተርፕራይዞች ያዘጋጀው የመስሪያ ቦታ ርክክብ ተደርጓል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025