
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦የህንድ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት መስክ የመሰማራት ፍላጎት እንዳላቸው አስታወቁ ።
በህንድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን መሪ አምባሳደር ሞላልኝ አስፋው ከህንዱ ፒኤችዲ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት እና ኬኤልጂ ግሩፕ ኦፍ ኢንዱስትሪስ ከተሰኘው አምራች ኩባንያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሽሪ ሄርማንት ጃን ጋር ተወያይተዋል።
ውይይቱ የኢትዮጵያ እና ህንድ የንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ማጠናከር ላይ ያተኮረ ነው።
አምባሳደር ሞላልኝ የኢትዮጵያን ብዝሃ የኢንቨስትመንት እድሎች አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ ያሉ አማራጮችን እንዲቃኝ ጥሪ አቅርበዋል።
ሽሪ ሄርማንት ጃን በምክር ቤቱ ስር ያሉ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸው እ.አ.አ ጁን 2025 የንግድ ልዑክ በኢትዮጵያ ጉብኝት እንደሚያደርግ ጠቁመዋል።
ከ130 ሺህ በላይ አባላት ያሉት ፒኤችዲ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት የህንድ ላኪዎችን የሚወክል ግዙፍ ተቋም መሆኑን በኒው ዴልሂ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ኬኤልጂ ግሩፕ ኦፍ ኢንዱስትሪስ በህንድ እና እስያ ግዙፍ የፕላስቲክ እና የፕላስቲክ ውጤቶች አምራች ኩባንያ ነው።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025