የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ ድጋፍ ያደርጋል

Apr 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ ስራዎች ድጋፍ ለማድረግ እንደሚሻ አስታወቀ።


የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)፥የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን የስራ ኃላፊዎችን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።


በኩታ-ገጠም የግብርና ልማት ስራዎችን ማስፋፋት፣ በግብርናው ዘርፍ የስራ ዕድል ፈጠራን ማስፋትና ዘርፉን በቴክኖሎጂ በመደገፍ እንዲዘምንና ሳቢ እንዲሆን በማድረግ ወጣቶችን ወደ ዘርፉ እንዲገቡ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።


እንዲሁም በግብርና ኢንቨስትመንት፣በገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት እና በሌሎች የግብርና ልማት ስራዎች ምርታማነትን ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይም ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል።


ሚኒስትሩ የግብርና ዘርፍ ስራን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን መንግስት ለዘርፉ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርናው ዘርፍ ትልቅ ዕድል እንደፈጠረ አመልክተዋል።


የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን የስራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ምርታማነትን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸውን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026