
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ ስራዎች ድጋፍ ለማድረግ እንደሚሻ አስታወቀ።
የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)፥የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን የስራ ኃላፊዎችን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
በኩታ-ገጠም የግብርና ልማት ስራዎችን ማስፋፋት፣ በግብርናው ዘርፍ የስራ ዕድል ፈጠራን ማስፋትና ዘርፉን በቴክኖሎጂ በመደገፍ እንዲዘምንና ሳቢ እንዲሆን በማድረግ ወጣቶችን ወደ ዘርፉ እንዲገቡ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።
እንዲሁም በግብርና ኢንቨስትመንት፣በገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት እና በሌሎች የግብርና ልማት ስራዎች ምርታማነትን ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይም ሀሳቦችን ተለዋውጠዋል።
ሚኒስትሩ የግብርና ዘርፍ ስራን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን መንግስት ለዘርፉ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለግብርናው ዘርፍ ትልቅ ዕድል እንደፈጠረ አመልክተዋል።
የቢል እና ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን የስራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ምርታማነትን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው መግለጻቸውን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026