አዶላ፤ ሚያዝያ 2/2017(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ160 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡
በዞኑ በየአመቱ ከመጋቢት 15 እስከ ሚያዝያ መጨረሻ የዝናብና የበልግ አዝመራ የዘር ወቅት ሲሆን በጉጂ ዞን ከሚገኙ 13 ወረዳዎች መካከል አዶላ ሬዴ፣ ዋደራ፣ ሰባቦሩ፣ ግርጃ፣ አጋ ወዩና ሻኪሶ በልግ አብቃይ እንደሆኑም ተጠቅሷል፡፡
የጽህፈት ቤቱ ምክትል ሀላፊ አቶ ቂልጣ ጂማ፤ ዘንድሮ በዞኑ የበልግ አዝመራ 254 ሺህ ሄክታር መሬት ታርሶ ለዘር ተዘጋጅቷል ብለዋል፡፡
በዞኑ ስድስት ወረዳዎች እስካሁን በተሰራው ስራ 162 ሺህ 560 ሄክታር መሬት በዋናነት በስንዴ፣ በቆሎ፣ ጤፍ፣ ገብስና ቦለቄ ዘር መሸፈኑን ገልጸዋል፡፡
በተያዘው ዓመት የበልግ አዝመራ ምርታማነትን የሚጨምሩ አዳዲስ የግብርና መካናይዜሽን አሰራሮች መመቻቸታቸውን ጠቅሰው በዚህም የኩታገጠም አስተራረስ ዘዴ፤ የአፈር ማዳበሪያና የምርጥ ዘር አቅርቦት ዋናዎቹ እንደሆኑም አስታውቀዋል፡፡
እንዲሁም በዞኑ እስካሁን 95 ሺህ 600 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያና 37 ሺህ 334 ኩንታል ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ መቅረቡን አስታውሰዋል፡፡
በበልግ አዝመራ ከሚለማው መሬትም 6 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልጸዋል፡፡
በዞኑ አዶላ ሬዴ ወረዳ የደራርቱ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አቶ ዳዴ ደርሶ፤ ከእንስሳት እርባታ ጎን ለጎን በበልግ አዝመራ ከተሳተፉ አርሶ አደሮች መካከል አንዱ ናቸው፡፡
ለበልግ አዝመራ ያዘጋጁትን አንድ ሄክታር መሬታቸውን በዘር መሸፈናቸውን ገልጸዋል፡፡
ለዘንድሮ በልግ አዝመራ ካዘጋጁት መሬት ከ30 ኩንታል በላይ የበቆሎ ምርት እንደሚጠብቁ አስታውቀዋል፡፡
የዚሁ ወረዳና ቀበሌ ነዋሪ ወጣት ወገኔ ክፍሌ ከሌሎች ስድስት አርሶ አደሮች ጋር በመተባበር ስድስት ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም አስተራረስ በዘር መሸፈናቸውን ገልጿል፡፡
''ከሰብሉም እስከ 180 ኩንታል የበቆሎ ምርት ለማግኘት አቅደን እየሰራን ነው'' ያለው ወጣቱ መንግስት የግብርና አሰራሮች በማመቻቸት ድጋፍና ክትትል እያደረገላቸው መሆኑን አሳውቋል፡፡
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025