ኢትዮጵያን ጨምሮ በሰባት የምስራቅ አፍሪካ አገራት ከመደበኛው በላይ ዝናብ የሚጠበቅ መሆኑን የምስራቅ አፍሪካ የአየር ሁኔታ መረጃ አገልግሎት (ኢክፓክ) አስታወቀ።
የኢክፓክ የቀጣዮቹ ስምንት ቀናት የአየር ትንበያ መረጃ እንደሚያመለክተው በምስራቅ አፍሪካ አገራት ከመደበኛው በላይ፣ መጠነኛ እና ዝቅተኛ የዝናብ ስርጭት የሚኖር ይሆናል።
በዚህም መሰረት የዝናብ ስርጭቱ በደቡብና ማእከላዊ ኢትዮጵያ፣ደቡብ ሱዳን፣ኡጋንዳ፣ሩዋንዳ፣ ብሩንዲ፣የታንዛኒያ ምእራባዊ ክፍል፣በኬኒያ በርካታ አካባቢዎች እና በሶማሊያ ደቡባዊ ክፍል ከመደበኛው ከፍ ያለ ዝናብ ይኖራል።
በታንዛኒያ አብዛኛው አካባቢዎች፣ሶማሊያ፣ጅቡቲ እና ኤርትራ፣ በኬኒያ ምስራቃዊ ክፍል፣ በደቡብ ሱዳን እና የሶማሊያ ደቡባዊ ክፍል ከፍተኛ የሙቀት መጠን እንደሚኖር ይጠበቃል።
በመሆኑም በእነዚህ አካባቢዎች የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት አመላክቷል።
የምስራቅ አፍሪካ የአየር ሁኔታ መረጃ አገልግሎት (ICPAC) በኢጋድ ስር ሆኖ የአየር ትንበያና ሌሎች ተያያዥ ተግባራትን የሚያከናውን ቀጣናዊ ተቋም መሆኑ ይታወቃል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025