
ኢትዮጵያን ጨምሮ በሰባት የምስራቅ አፍሪካ አገራት ከመደበኛው በላይ ዝናብ የሚጠበቅ መሆኑን የምስራቅ አፍሪካ የአየር ሁኔታ መረጃ አገልግሎት (ኢክፓክ) አስታወቀ።
የኢክፓክ የቀጣዮቹ ስምንት ቀናት የአየር ትንበያ መረጃ እንደሚያመለክተው በምስራቅ አፍሪካ አገራት ከመደበኛው በላይ፣ መጠነኛ እና ዝቅተኛ የዝናብ ስርጭት የሚኖር ይሆናል።
በዚህም መሰረት የዝናብ ስርጭቱ በደቡብና ማእከላዊ ኢትዮጵያ፣ደቡብ ሱዳን፣ኡጋንዳ፣ሩዋንዳ፣ ብሩንዲ፣የታንዛኒያ ምእራባዊ ክፍል፣በኬኒያ በርካታ አካባቢዎች እና በሶማሊያ ደቡባዊ ክፍል ከመደበኛው ከፍ ያለ ዝናብ ይኖራል።
በታንዛኒያ አብዛኛው አካባቢዎች፣ሶማሊያ፣ጅቡቲ እና ኤርትራ፣ በኬኒያ ምስራቃዊ ክፍል፣ በደቡብ ሱዳን እና የሶማሊያ ደቡባዊ ክፍል ከፍተኛ የሙቀት መጠን እንደሚኖር ይጠበቃል።
በመሆኑም በእነዚህ አካባቢዎች የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት አመላክቷል።
የምስራቅ አፍሪካ የአየር ሁኔታ መረጃ አገልግሎት (ICPAC) በኢጋድ ስር ሆኖ የአየር ትንበያና ሌሎች ተያያዥ ተግባራትን የሚያከናውን ቀጣናዊ ተቋም መሆኑ ይታወቃል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026