የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኢትዮጵያን ጨምሮ በሰባት የምስራቅ አፍሪካ አገራት ከመደበኛው በላይ ዝናብ ይጠበቃል

Apr 11, 2025

IDOPRESS

ኢትዮጵያን ጨምሮ በሰባት የምስራቅ አፍሪካ አገራት ከመደበኛው በላይ ዝናብ የሚጠበቅ መሆኑን የምስራቅ አፍሪካ የአየር ሁኔታ መረጃ አገልግሎት (ኢክፓክ) አስታወቀ።


የኢክፓክ የቀጣዮቹ ስምንት ቀናት የአየር ትንበያ መረጃ እንደሚያመለክተው በምስራቅ አፍሪካ አገራት ከመደበኛው በላይ፣ መጠነኛ እና ዝቅተኛ የዝናብ ስርጭት የሚኖር ይሆናል።


በዚህም መሰረት የዝናብ ስርጭቱ በደቡብና ማእከላዊ ኢትዮጵያ፣ደቡብ ሱዳን፣ኡጋንዳ፣ሩዋንዳ፣ ብሩንዲ፣የታንዛኒያ ምእራባዊ ክፍል፣በኬኒያ በርካታ አካባቢዎች እና በሶማሊያ ደቡባዊ ክፍል ከመደበኛው ከፍ ያለ ዝናብ ይኖራል።


በታንዛኒያ አብዛኛው አካባቢዎች፣ሶማሊያ፣ጅቡቲ እና ኤርትራ፣ በኬኒያ ምስራቃዊ ክፍል፣ በደቡብ ሱዳን እና የሶማሊያ ደቡባዊ ክፍል ከፍተኛ የሙቀት መጠን እንደሚኖር ይጠበቃል።


በመሆኑም በእነዚህ አካባቢዎች የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት አመላክቷል።


የምስራቅ አፍሪካ የአየር ሁኔታ መረጃ አገልግሎት (ICPAC) በኢጋድ ስር ሆኖ የአየር ትንበያና ሌሎች ተያያዥ ተግባራትን የሚያከናውን ቀጣናዊ ተቋም መሆኑ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026