
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 4/2017(ኢዜአ)፦ በ2017 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት 160 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሰውነት አየለ በሰጡት መግለጫ፥ ቢሮው የገቢ መሰብሰብ አቅሙን ለማሳደግ ባከናወናቸው ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶች ማስመዝገቡን ገልጸዋል።
ከተማዋ ከምታመነጨው ኢኮኖሚ ተገቢውን ገቢ በመሰብሰብ የከተማ አስተዳደሩ የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት የሚያደርገውን ጥረት ለማሳካት እየተጋ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 163 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ 160 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።
አገልግሎት አሰጣጡን ለማቀላጠፍ፣ ብልሹ አሰራሮችንና ሌብነትን ለመቅረፍ የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ሥራ በማስገባት የገቢ አሰባሰቡን እያሻሻለ መምጣቱንም ነው ያነሱት።
የዕዳ ክትትልና አስተዳደርን በማጠናከር በዘጠኝ ወራት ብቻ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ዕዳ መሰብሰቡን አንስተው፥ የታክስ ስወራን ለመቀነስ እየተሰራ ነው ብለዋል።
አዲስ የኦዲት ጥናት አረጋጋጭ የስራ ክፍል በማደራጀት በኦዲተሮች የሚወሰኑ ውሳኔዎችን በድጋሚ ኦዲት በማድረግና የኦዲት ጥራት በማረጋገጥና ብልሹ አሰራሮችን በመቀነስ የከተማዋ ገቢ እንዲጨምር እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
የገቢ አሰባሰብ ሂደት ላይ የስነ ምግባር ጉድለትና ብልሹ አሰራር የፈጸሙ 12 አመራሮች እና 121 ፈጻሚዎች ላይ እርምጃ መውሰዱንም ገልጸዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026