
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 4/2017(ኢዜአ)፦ በ2017 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት 160 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሰውነት አየለ በሰጡት መግለጫ፥ ቢሮው የገቢ መሰብሰብ አቅሙን ለማሳደግ ባከናወናቸው ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶች ማስመዝገቡን ገልጸዋል።
ከተማዋ ከምታመነጨው ኢኮኖሚ ተገቢውን ገቢ በመሰብሰብ የከተማ አስተዳደሩ የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት የሚያደርገውን ጥረት ለማሳካት እየተጋ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 163 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ 160 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።
አገልግሎት አሰጣጡን ለማቀላጠፍ፣ ብልሹ አሰራሮችንና ሌብነትን ለመቅረፍ የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ሥራ በማስገባት የገቢ አሰባሰቡን እያሻሻለ መምጣቱንም ነው ያነሱት።
የዕዳ ክትትልና አስተዳደርን በማጠናከር በዘጠኝ ወራት ብቻ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ዕዳ መሰብሰቡን አንስተው፥ የታክስ ስወራን ለመቀነስ እየተሰራ ነው ብለዋል።
አዲስ የኦዲት ጥናት አረጋጋጭ የስራ ክፍል በማደራጀት በኦዲተሮች የሚወሰኑ ውሳኔዎችን በድጋሚ ኦዲት በማድረግና የኦዲት ጥራት በማረጋገጥና ብልሹ አሰራሮችን በመቀነስ የከተማዋ ገቢ እንዲጨምር እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
የገቢ አሰባሰብ ሂደት ላይ የስነ ምግባር ጉድለትና ብልሹ አሰራር የፈጸሙ 12 አመራሮች እና 121 ፈጻሚዎች ላይ እርምጃ መውሰዱንም ገልጸዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025