
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 4/2017(ኢዜአ)፦ በ2017 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት 160 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሰውነት አየለ በሰጡት መግለጫ፥ ቢሮው የገቢ መሰብሰብ አቅሙን ለማሳደግ ባከናወናቸው ተግባራት ተጨባጭ ውጤቶች ማስመዝገቡን ገልጸዋል።
ከተማዋ ከምታመነጨው ኢኮኖሚ ተገቢውን ገቢ በመሰብሰብ የከተማ አስተዳደሩ የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት የሚያደርገውን ጥረት ለማሳካት እየተጋ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 163 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ 160 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ተናግረዋል።
አገልግሎት አሰጣጡን ለማቀላጠፍ፣ ብልሹ አሰራሮችንና ሌብነትን ለመቅረፍ የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ሥራ በማስገባት የገቢ አሰባሰቡን እያሻሻለ መምጣቱንም ነው ያነሱት።
የዕዳ ክትትልና አስተዳደርን በማጠናከር በዘጠኝ ወራት ብቻ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ዕዳ መሰብሰቡን አንስተው፥ የታክስ ስወራን ለመቀነስ እየተሰራ ነው ብለዋል።
አዲስ የኦዲት ጥናት አረጋጋጭ የስራ ክፍል በማደራጀት በኦዲተሮች የሚወሰኑ ውሳኔዎችን በድጋሚ ኦዲት በማድረግና የኦዲት ጥራት በማረጋገጥና ብልሹ አሰራሮችን በመቀነስ የከተማዋ ገቢ እንዲጨምር እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
የገቢ አሰባሰብ ሂደት ላይ የስነ ምግባር ጉድለትና ብልሹ አሰራር የፈጸሙ 12 አመራሮች እና 121 ፈጻሚዎች ላይ እርምጃ መውሰዱንም ገልጸዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026