
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማቱ መንገዶች ለሚፈለገው ዓላማ እንዲውሉ በማድረግ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑ ተገልጿል።
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች በአዲስ አበባ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ የኮሪደር ልማቶችን፣ ብሔራዊ ቤተ-መንግስትንና አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡

በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የሚኒስትር ዴዔታ አማካሪ ቶሎሳ ፉፋ(ዶ/ር) ጉብኝቱን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚከናወኑ መሰረተ ልማቶች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው።
በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ በመቀየርና ዘመናዊ አኗኗርን በማስረጽ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አመራሮችና ሰራተኞች ያደረጉት ጉብኝትም በከተማዋ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ለመመልከት እድል የፈጠረ ነው ብለዋል።
በከተማዋ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የመንግስትን የመፈጸም አቅምና ቁርጠኝነት የሚያሳዩ ከመሆናቸው ባሻገር ለከተማዋ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ጉልህ አስተዋጽኦ ያላቸው መሆናቸውን አንስተዋል።
በጉብኝቱ የተመለከቷቸው ፕሮጀክቶች በአጭር ግዜ ውስጥ ግንባታቸው ተጠናቆ አገልገሎት መስጠት የጀመሩ መሆናቸው ደግሞ በእጅጉ የሚደነቅ ነው ብለዋል።
በከተማዋ የኮሪደር ልማት ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የተገነባ መሆኑ ለትራንስፖርት ዘርፉ ያለው ፋይዳ ትልቅ መሆኑንም ገልጸዋል።

በዋናነት የኮሪደር ልማቱ መንገዶች ለታለመላቸው ዓላማ በማዋል ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ስትራቴጂ ጋር የተጣጣመ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026