
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማቱ መንገዶች ለሚፈለገው ዓላማ እንዲውሉ በማድረግ በኩል ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑ ተገልጿል።
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች በአዲስ አበባ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ የኮሪደር ልማቶችን፣ ብሔራዊ ቤተ-መንግስትንና አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡

በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የሚኒስትር ዴዔታ አማካሪ ቶሎሳ ፉፋ(ዶ/ር) ጉብኝቱን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚከናወኑ መሰረተ ልማቶች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው።
በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ በመቀየርና ዘመናዊ አኗኗርን በማስረጽ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አመራሮችና ሰራተኞች ያደረጉት ጉብኝትም በከተማዋ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ለመመልከት እድል የፈጠረ ነው ብለዋል።
በከተማዋ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የመንግስትን የመፈጸም አቅምና ቁርጠኝነት የሚያሳዩ ከመሆናቸው ባሻገር ለከተማዋ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ጉልህ አስተዋጽኦ ያላቸው መሆናቸውን አንስተዋል።
በጉብኝቱ የተመለከቷቸው ፕሮጀክቶች በአጭር ግዜ ውስጥ ግንባታቸው ተጠናቆ አገልገሎት መስጠት የጀመሩ መሆናቸው ደግሞ በእጅጉ የሚደነቅ ነው ብለዋል።
በከተማዋ የኮሪደር ልማት ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የተገነባ መሆኑ ለትራንስፖርት ዘርፉ ያለው ፋይዳ ትልቅ መሆኑንም ገልጸዋል።

በዋናነት የኮሪደር ልማቱ መንገዶች ለታለመላቸው ዓላማ በማዋል ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ስትራቴጂ ጋር የተጣጣመ መሆኑን ተናግረዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026