የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ዝነኛው ፒያኒስት ግርማ ይፍራሸዋ የዓለም የክላሲካል ሙዚቃ አዋርድ ሽልማት አገኘ 

Apr 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ሚያዚያ 8/2017(ኢዜአ):- ዝነኛው ፒያኒስት ግርማ ይፍራሸዋ በሩሲያ ሞስኮ በተካሄደው “ብራቮ አዋርድ” በተሰኘ የዓለም የክላሲካል ሙዚቃ አዋርድ በክላሲካል ሙዚቃ ዘርፍ ሽልማት አግኝቷል።

ስነ ስርዓቱ በሞስኮ ጥንታዊው ቦልሾል ቴአትር አዳራሽ ተከናውኗል።

በሽልማቱ ላይ የብሪክስ አባል እና አጋር ሀገራት ከሆኑት ሩሲያ፣ ቻይና፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ህንድ፣ ሰርቢያ እና ቤላሩስ የተወጣጡ ታዋቂ ሙዚቀኞች፣ የሙዚቃ ባለሙያዎች፣ ደራሲዎች፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች እና የዘርፉ ተዋንያን ተገኝተዋል።


በሁነቱ ላይ የታደሙት በሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ገነት ተሾመ (ዶ/ር) ለዝነኛው ፒያኒስት ግርማ ይፍራሸዋ ለተበረከተለት ሽልማት የእንኳን ደስ አለህ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ፒያኒስቱ ኢትዮጵያ ለሩሲያ ህዝብ በማስተዋወቅ ለተወጣው ሚና ያላቸውን አድናቆታቸውን ገልጸዋል።

አምባሳደር ገነት የሽልማቱ አዘጋጆች ኢትዮጵያ ለሙዚቃ እና ለባህል ልውውጥ እያበረከተች ላለው አስተዋጽኦ ለሰጡት እውቅና ምስጋና ማቅረባቸውን በሞስኮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026