የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የቀድሞው ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ሃይለማርያምን አውሮፕላን ጠግኖ ለአገልግሎት ማብቃት በሁሉም መስክ ውጤታማ ስራ የማከናወን ማሳያ ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

Apr 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 8/2017(ኢዜአ)፦ የቀድሞው ፕሬዝዳንት አውሮፕላን ከ37 ዓመታት በኋላ ጠግኖ ለአገልግሎት ማብቃት በተቋሙ በሁሉም መስክ ውጤታማ ሥራ እየተሠራ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ።

ከአገልግሎት ውጪ የነበረውን የቀድሞው ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ሃይለ ማርያም አውሮፕላን ጠግኖ ጥቅም ላይ ማዋል መቻሉ ተገልጿል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ እንደገለጹት የቀድሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ሃይለማርያም አውሮፕላን ከተጣለበት ጥሻ በማንሳት አፕግሬድና ኦቨር ሆል በማድረግ ከ37 ዓመት በኋላ የበረራ አገልግሎት እንዲሠጥ ማድረግ ተችሏል።


ይሄም በመከላከያ ሰራዊት ተቋም ውስጥ በሁሉም መስክ ውጤታማ ሥራ እየተሠራ ስለመሆኑ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።

አውሮፕላኑ አስፈላጊውን ጥገና አግኝቶ መብረር እና ወደ ኃይል መመለስ እንዲችል በሰጠነው መመሪያ መሠረት ለተሳተፋችሁ የአየር ሃይል አመራሮች ቴክኒሺያኖች የመከላከያ ድጋፍ ሰጪ ሁሉ አመሠግናለሁ ብለዋል።

የኢፌዴሪ አየር ሃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ በበኩላቸው አየር ሃይል በሰው ሃይል ግንባታ ፣ትጥቆችን ማሣደግና ከዘመኑ አቅም ላይ ማድረስ፣ መሠረተ ልማቶችን ተቋሙን በሚመጥን ልክ ማስፋፋት ትኩረት የተሠጠባቸው መሠረታዊ ነጥቦች መሆናቸውን ገልጸዋል።


አውሮፕላኑን ጠግኖ ወደ ኃይል መመለስም የዚሁ አንድ አካል ነው ብለዋል።

ዳሽ ፋይፍ ወይም ቡፋሎ በሚል መጠሪያ የሚታወቀውና ለቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም አገልግሎት ይሠጥ የነበረውን አውሮፕላን ከአንድ ዓመት ጊዜ በላይ አስፈላጊውን ጥገና በአየር ሃይል ቴክኒሺያኖች በመሥጠት ከሰላሣ ሰባት ዓመታት በኋላ ለበረራ ማብቃት እንደተቻለም ተናግረዋል።

ለትራንስፖርት ፣ለፓራሹት ዝላይ እና የካርጎ አገልግሎት መሥጠት የሚችለው አውሮፕላን ተጠግኖ ወደ ኃይል እንዲመለስ የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ለሠጡት ድጋፍ ሙያተኞች ላደረጉት አበርክቶ ዋና አዛዡ ማመስገናቸውን ከመከላከያ ሰራዊት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026