
ጋምቤላ፤ሚያዝያ 9/2017 (ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እያደረገ ያለው የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን( ዶ.ር) ገለፁ።
በጋምቤላ ከተማ አስተዳደር የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ለከተማው ተጠቃሚዎች ተጨማሪ የአካባቢ ልማት ስራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሂዷል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ(ዶ/ር) በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ እንዳሉት፥ የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮግራም ነው።
በክልሉ በሚገኙ ከተሞች የመስራት አቅም እያላቸው መነሻ ድጋፍ ያላገኙ ዜጎችን በፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እደሚቀጥልም ገልፀዋል።
የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሳይመን ሙን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ መንግስት በከተሞች ያለውን የድህነት ምጣኔ ለመቀነስና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም የተጠቃሚዎችን ኑሮ በዘላቂነት ከማሻሻል ባለፈ የከተማን ገጽታ በመገንባት ረገድ የላቀ አበርክቶ አለው ብለዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026