ጋምቤላ፤ሚያዝያ 9/2017 (ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እያደረገ ያለው የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን( ዶ.ር) ገለፁ።
በጋምቤላ ከተማ አስተዳደር የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ለከተማው ተጠቃሚዎች ተጨማሪ የአካባቢ ልማት ስራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሂዷል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ(ዶ/ር) በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ እንዳሉት፥ የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮግራም ነው።
በክልሉ በሚገኙ ከተሞች የመስራት አቅም እያላቸው መነሻ ድጋፍ ያላገኙ ዜጎችን በፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እደሚቀጥልም ገልፀዋል።
የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሳይመን ሙን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ መንግስት በከተሞች ያለውን የድህነት ምጣኔ ለመቀነስና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም የተጠቃሚዎችን ኑሮ በዘላቂነት ከማሻሻል ባለፈ የከተማን ገጽታ በመገንባት ረገድ የላቀ አበርክቶ አለው ብለዋል።
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025