
ጋምቤላ፤ሚያዝያ 9/2017 (ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እያደረገ ያለው የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን( ዶ.ር) ገለፁ።
በጋምቤላ ከተማ አስተዳደር የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ለከተማው ተጠቃሚዎች ተጨማሪ የአካባቢ ልማት ስራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሂዷል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ(ዶ/ር) በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ እንዳሉት፥ የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮግራም ነው።
በክልሉ በሚገኙ ከተሞች የመስራት አቅም እያላቸው መነሻ ድጋፍ ያላገኙ ዜጎችን በፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እደሚቀጥልም ገልፀዋል።
የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሳይመን ሙን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ መንግስት በከተሞች ያለውን የድህነት ምጣኔ ለመቀነስና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም የተጠቃሚዎችን ኑሮ በዘላቂነት ከማሻሻል ባለፈ የከተማን ገጽታ በመገንባት ረገድ የላቀ አበርክቶ አለው ብለዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025