
ጋምቤላ፤ሚያዝያ 9/2017 (ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እያደረገ ያለው የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን( ዶ.ር) ገለፁ።
በጋምቤላ ከተማ አስተዳደር የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ለከተማው ተጠቃሚዎች ተጨማሪ የአካባቢ ልማት ስራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሂዷል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ(ዶ/ር) በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ እንዳሉት፥ የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮግራም ነው።
በክልሉ በሚገኙ ከተሞች የመስራት አቅም እያላቸው መነሻ ድጋፍ ያላገኙ ዜጎችን በፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እደሚቀጥልም ገልፀዋል።
የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሳይመን ሙን (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ መንግስት በከተሞች ያለውን የድህነት ምጣኔ ለመቀነስና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም የተጠቃሚዎችን ኑሮ በዘላቂነት ከማሻሻል ባለፈ የከተማን ገጽታ በመገንባት ረገድ የላቀ አበርክቶ አለው ብለዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026