የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ በየትኛውም መስፈርት የሀገርና ህዝብን ህልውና መሰረት ያደረገ ጥያቄ ነው

Apr 24, 2025

IDOPRESS

ጂንካ ፤ሚያዚያ 15/2017 (ኢዜአ) :- የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ በየትኛውም መስፈርት የሀገርና ህዝብን ህልውና መሰረት ያደረገ ጥያቄ መሆኑ ተገለጸ።

በዓለም ላይ የባህር በር የሌላቸው አገራት በዓለም አቀፍ ህግ መሰረት በሰጥቶ መቀበል መርህ እና ሌሎችም አማራጮች በስምምነት የባህር በር ተጠቃሚ መሆናቸው ይታወቃል።

በሁለትዮሽ፣ በቀጣናዊና አህጉራዊ ደረጃ ስምምነቶችን በማድረግ የባህር በር ተጠቃሚ በመሆን የጋራ ተጠቃሚነትን የእድገት አማራጭ ማድረግ የቻሉ አገራት በርካቶች ናቸው።

ለአብነትም አፍጋኒስታን ከፓኪስታን ጋር እንዲሁም የላቲን አሜሪካዋ ቦሊቪያ ከፔሩ ጋር በመስማማት የባህር በር ባለቤት መሆን ችለዋል።

ከቀይ ባህር በቅርብ ርቀት ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት የነበረች ቢሆንም በታሪክ አጋጣሚ የቅርብ ተመልካች እንድትሆን ተደርጋለች።

በመሆኑም አሁን ላይ መንግስት ኢትዮጵያ የባህር በር ሊኖራት ይገባል የሚል ጠንካራ አቋም በመያዝ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቱን አጠናክሮ መቀጠሉ ይታወቃል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን የኢትዮጵያ የባህር በር ጉዳይ በየትኛውም መስፈርት የሀገርና ህዝብን ህልውና መሰረት ያደረገ ጥያቄ መሆኑን አንስተዋል።

ኢትዮጵያ በቅርበት እያለች አጥታ የቆየችውን የባህር በር ለማግኘት መንግስት እያደረገ ያለው የዲፕሎማሲ ጥረትም የሚደነቅ ነው ብለዋል።

በዩኒቨርሲቲው የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር ትምህርት መምህር ምስክር ከተማ፤ የኢትዮጵያ ባህር በር ጉዳይ ሳይነሳ በዝምታ ለበርካታ ዓመታት በዝምታ መቆየቱ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም የዘነጋ ነበር ሲሉ አንስተዋል።

በመሆኑም ለውጡን ተከትሎ መንግስት የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ ነው ብሎ መነሳቱ ከምንም በላይ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም መቆሙን የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ የመንግስትን ጥረት ሁላችንም የማገዝና የመደገፍ ኃላፊነት አለብን ብለዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽ የሚሻ በመሆኑ በተለይም ምሁራን፣ ታዋቂ ግለሰቦችና በማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ጉዳዩን አጀንዳ አድርገው መያዝ ያለባቸው መሆኑን አንስተዋል።


በዩኒቨርሲቲው የታሪክና ቅርስ አስተዳደር ክፍል ኃላፊና የታሪክ መምህሩ ወንድማገኝ ነጋሽ፤ ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚ የባህር በር ማጣቷ ለሁላችንም ቁጭት ፈጥሮብን ቆይቷል ብለዋል።

በመሆኑም አሁን ላይ ጥያቄው መነሳቱ በየትኛውም መስፈርት የሀገርና የህዝብን ህልውና መሰረት ያደረገ ጥያቄ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ የትውልዱ መሆኑን አንስተው ለምላሹ መሳካት በጋራ ቆሞ መስራት የሚገባ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህ ረገድ በተለይም ምሁራን፣ የማህበረሰብ አንቂዎች፣ ታዋቂና ተፅእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እና የዳያስፖራ አባላት የሁልጊዜም ጥያቄያቸው አድርገው ሊይዙት ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026