
ጭሮ ፤ሚያዝያ 16/2017 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ከለማው መሬት ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የዞኑ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
በዞኑ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ሀቢብ አብዱልከሪም ለኢዜአ እንደገለጹት የስንዴ ምርቱ የተሰበሰበው በዞኑ 15 ወረዳዎች ከለማው ከ65 ሺህ 413 ሄክታር መሬት ላይ ነው፡፡
የምርት መጠኑም ባለፈው አመት ከተገኘው ከ500 ሺህ ኩንታል በላይ ብልጫ እንዳለው አመልክተው የተቀረው 414 ሄክታር መሬት ላይ ያለው ሰብል እስከተያዘው ወር መጨረሻ እንደሚሰበሰብ ጠቁመዋል፡፡

በዞኑ በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በ15 ወረዳዎች የሚገኙ ከ240 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውንም አስታውሰዋል።
የዞኑ አርሶ አደሮች በዩኒየኖቹ በኩል ምርታቸውን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
በቦኬ ወረዳ ቦኬ ሀሮ ዱዳ ቀበሌ አርሶ አደር ከድር ዩሱፍ እንዳሉት ከግማሽ ሄክታር በላይ ማሳ በበጋ መስኖ ስንዴ ካለሙት መሬት አብዛኛውን በመሰብሰብ 16 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።
ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ በመሸጥ እያገኙ ያለው ገቢ የምርት ማሳደጊያ ግብአቶችን በበቂ ሁኔታ ለመግዛት እንዳስቻላቸው የተናገሩት ደግሞ ሌላኛው የቀበሌው ነዋሪ አርሶ አደር አብዱል አዚዝ መሀመድ ናቸው፡፡
በቀጣይ በልማቱ በንቃት በመሳተፍ ምርታማነታቸውን ለማሳደግ እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026