
ጭሮ ፤ሚያዝያ 16/2017 (ኢዜአ)፡-በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ከለማው መሬት ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የዞኑ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
በዞኑ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ሀቢብ አብዱልከሪም ለኢዜአ እንደገለጹት የስንዴ ምርቱ የተሰበሰበው በዞኑ 15 ወረዳዎች ከለማው ከ65 ሺህ 413 ሄክታር መሬት ላይ ነው፡፡
የምርት መጠኑም ባለፈው አመት ከተገኘው ከ500 ሺህ ኩንታል በላይ ብልጫ እንዳለው አመልክተው የተቀረው 414 ሄክታር መሬት ላይ ያለው ሰብል እስከተያዘው ወር መጨረሻ እንደሚሰበሰብ ጠቁመዋል፡፡

በዞኑ በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት በ15 ወረዳዎች የሚገኙ ከ240 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውንም አስታውሰዋል።
የዞኑ አርሶ አደሮች በዩኒየኖቹ በኩል ምርታቸውን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
በቦኬ ወረዳ ቦኬ ሀሮ ዱዳ ቀበሌ አርሶ አደር ከድር ዩሱፍ እንዳሉት ከግማሽ ሄክታር በላይ ማሳ በበጋ መስኖ ስንዴ ካለሙት መሬት አብዛኛውን በመሰብሰብ 16 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።
ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ በመሸጥ እያገኙ ያለው ገቢ የምርት ማሳደጊያ ግብአቶችን በበቂ ሁኔታ ለመግዛት እንዳስቻላቸው የተናገሩት ደግሞ ሌላኛው የቀበሌው ነዋሪ አርሶ አደር አብዱል አዚዝ መሀመድ ናቸው፡፡
በቀጣይ በልማቱ በንቃት በመሳተፍ ምርታማነታቸውን ለማሳደግ እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026