የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ለሁለት ቀናት ያካሔደውን ጉባኤ መጠናቀቅ ተከትሎ ባወጣው መግለጫ ላይ ከኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ከተጠቀሱት ዋና ዋና ነጥቦች መካከል ፦
በያዝነው አመት አጠቃላይ ኢኮኖሚው በታቀደው መሠረት በ8 ነጥብ 4 በመቶ የሚያድግ መሆኑን የሥራ አስፈጻሚው ገምግሟል፡፡
ግብርና በ6 ነጥብ 1 በመቶ፣ ኢንዱስትሪ በ12ነጥብ 8 በመቶ፣ ማኑፋክቸሪንግ በ12 በመቶ፣ ኮንስትራክሽን በ12 ነጥብ 3 በመቶ፣ አገልግሎት ደግሞ በ7 ነጥብ 1 በመቶ የሚያድጉ መሆናቸው ተገምግሟል፡፡
ያለፉት 9 ወራት ጠቅላላ የመንግሥት ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት አንጻር የ134 በመቶ ብልጫ አሳይቷል፡፡ የውጭ ብድር ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ያለው ድርሻ ወደ 13 ነጥብ 7 በመቶ ወርዷል፡፡
ወደ ውጭ ገበያ የሚቀርቡት ስድስት ዋና ዋና ምርቶች፣ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸሩ ከ82 በመቶ እስከ 386 በመቶ ጭማሪ አሳይተዋል፡፡
በስንዴ፣ በሩዝ፣ በቡና፣ በሻይ ቅጠል እና በፍራፍሬ ምርቶች በአፍሪካ ቀዳሚ ሆኖ ለመውጣት እየተደረገ ያለው ትግል ፍሬ እያፈራ መሆኑን አይተናል፡፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ዝቅተኛ ኑሮ በሚኖሩ ወገኖች ላይ ጫና እንዳያሳድር አስፈላጊ የሆኑና የታቀዱ የድጋፍ መርሐ ግብሮች መከናወናቸውንም የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው መርምሯል፡፡
ለማዳበሪያ 62 ቢሊዮን ብር፣ ለሴፍቲኔት 41 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር፣ ለነዳጅ 60 ቢሊዮን ብር፣ ለመድኃኒት 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር፣ ለምግብ ዘይት 6 ነጥብ1 ቢሊዮን ብር፣ እንዲሁም ለደመወዝ 38 ነጥብ 4 ቢሊ ዮን ብር ድጎማ ተደርጓል፡፡
ባለፉት 9 ወራት ብቻ 344 ሺህ 790 የውጭ ሀገር ሕጋዊ የሥራ ዕድሎች እና ከ3 ሚሊዮን በላይ የሀገር ውስጥ የሥራ ዕድሎች ተፈጥረዋል፡፡
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት የሚያግዙ ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የገበያ ማዕከላት ግንባታ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- በሚቀጥሉት አምስት አመታት በወረቀት የሚካሔዱ አሰራሮችን በማስቀረት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግብይትና አገልግሎት በተሻለ ...
Feb 8, 2025