
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 27/2017 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያን ነፃነት ለማስጠበቅ የተከፈለውን መስዋዕትነት ትውልዱ በልማት ስኬት መድገም እንደሚገባው አባት አርበኞች አስገነዘቡ።
አባት አርበኞች ዛሬ ሶስተኛውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ ላይ የተገኙት አርበኛ አስማማው መከተ፥ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ትውልዱ የሚያኮራ ታሪክ እየሰራ መሆኑን መመልከታቸውን ገልጸዋል።
በኤክስፖው በተለይም የስራ እድል መፍጠር የሚችሉና ሀገሪቱን ሊያሻግሩ የሚችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን በተጨባጭ ተመልክተናል ነው ያሉት።
ሻምበል አበበ አለሙ በበኩላቸው፥በተለያዩ አውደ ውጊያዎች በመሳተፍ አኩሪ ገድል ማስመዝገባቸውን አስታውሰው፤ የአሁኑ ትውልድ በልማት የራሱን የጀግንነት ታሪክ እየፃፈ መሆኑን መገንዘባቸውን ተናግረዋል።
አባት አርበኞቹ የኢትዮጵያን ነፃነት ለማስጠበቅ የተከፈለውን መስዋዕትነት በልማት ስኬት መድገም እንደሚገባ ገልጸዋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በበኩላችው፥ ጀግኖች አርበኞች የሀገራቸውን ዳር ድንበር ለማስከበር የከፈሉት መስዋዕትነት ለኢትዮጵያዊያን ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን ተናግረዋል።
የአሁኑ ትውልድ ኢትዮጵያን ከድሕነት ሊያወጡ በሚችሉ የልማት ተግባራት ላይ በመሳተፍ የሀገሩን ብልጽግና ማረጋገጥ ይጠበቅበታል ብለዋል።
አባት አርበኞች በዘመናቸው የራሳቸውን የጀግንነት ገድል እንደፈፀሙ ሁሉ ቀጣዩ ትውልድ የራሱ የሆነና የሚኮራበትን ታሪክ መስራት አለበት ብለዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ እውን ማድረግ ይገባል ያሉት ሚኒስትሩ፥ የአሁኑ ትውልድ አርበኝነት ከምርታማነት ጋር መያያዝ እንዳለበትም ነው ያስገነዘቡት፡፡
በተለይም ኋላቀርነትን በማስወገድ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ ምርት በማምረት ድሕነትን መዋጋት እንደሚገባም ጠቅሰዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የተዘጋጀውን ሦስተኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በይፋ መክፈታቸው ይታወሳል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025