
ጊምቢ፤ሚያዝያ 28/2017 (ኢዜአ)፦በምዕራብ ወለጋ ዞን በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከ2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የዞኑ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ገለጸ።
የምዕራብ ወለጋ ዞን ገቢዎች ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ገረመው ታደሰ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከተለያዩ የገቢ ምንጮች 2 ቢሊዮን 751 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል።
የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ5 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ ብልጫ እንዳለውም ገልጸዋል።
በዞኑ የሰፈነው ሰላም በተለይም ለንግዱ ማህብረሰብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ ነጋዴው ግብሩን በአግባቡ እንዲከፍል ማስቻሉ ደግሞ ገቢው በዚህ ልክ ለመሰብሰቡ እንደዋነኛ ምክንያት ጠቅሰዋል።
እንዲሁም የጽህፈት ቤቱ ሠራተኞችና አመራሮች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ገቢን በአግባቡ ለመሰብሰብ ባደረጉት ቅንጅታዊ ጥረት ገቢው ሊሰበሰብ መቻሉን ተናግረዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ የግብርና የታክስ ሕጎችን ተረድተው ግብራቸውን በጊዜ መክፈል እንዲችሉ በጽሕፈት ቤታቸዉ በተለያዩ ጊዜያት ስልጠናና የውይይት መድረኮች መዘጋጀታቸውንም ገልጸዋል።
በተለይም በተያዘው በጀት ዓመት ግብር ከፋዮች በጊዜ እንዲስተናገዱ በቴክኖሎጂ የታገዘ የግብር አሰባሰብ ስርዓት መዘርጋቱን ሃላፊው አስረድተዋል።
የመንግስትን ታክስና ግብር በጊዜና በታማኝነት መክፈል የልማት ስራዎች እንዲፋጠኑ ያስችላል።
በመሆኑም ሁሉም ግብሩን በወቅቱና በታማኝነት በመክፍል የድርሻውን እንዲወጣ አቶ ገረመው አሳስበዋል፡፡
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026