የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የኢትዮጵያ የማምረት አቅም ማደጉን ያየንበት ነው - የተለያዩ ሀገራት ዲፕሎማቶች

May 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የኢትዮጵያ የማምረት አቅም ማደጉን ያየንበት ነው ሲሉ ተቀማጭነታቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት ዲፕሎማቶች ተናገሩ።

ኢትዮጵያ በትክክለኛው የእድገት ጎዳና ላይ መሆኗን መገንዘባቸውንም ዲፕሎማቶቹ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ሚያዚያ 25 በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በይፋ ተመርቆ መከፈቱ ይታወቃል።

እየተካሄደ በሚገኘው ኤክስፖ ላይ 288 አምራቾች ምርታቸውን አቅርበው በማስጎብኘት ላይ ሲሆኑ በነገው እለትም የሚጠናቀቅ ይሆናል።

ተቀማጭነታቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት ዲፕሎማቶች በኤክስፖው የቀረቡ ምርቶችን ዛሬ ጎብኝተዋል።

ከጎብኚዎቹ መካከል በኢትዮጵያ የፖርቹጋል አምባሳደር ሊዊሳ ፍራጎሶ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኤክስፖው ኢትዮጵያ ወደ ኢንዱስትሪ ሽግግር ለማድረግ እየተገበረቻቸው ያሉ ኢኒሼቲቮች ውጤታማ መሆናቸውን ያየሁበት ነው ብለዋል።

በኤክስፖው ላይ የቀረቡ የምርቶች ስብጥር እንዲሁም ብዛት የኢትዮጵያ የማምረት አቅም እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ መሆኑንም ገልጸዋል።

ፖርቹጋል ከኢትዮጵያ ጋር ትብብሯን ማጠናከር እንደምትፈልግ የገለጹት አምባሳደር ሊዊሳ የፖርቹጋል ኩባንያዎች ከኢትዮጵያ ኩባንያዎች ጋር ይበልጥ ተቀራርበው እንዲሰሩ ፍላጎት አለን ብለዋል።

ይህንንም እውን ለማድረግ በጋራ እንሰራለን ነው ያሉት።

በሀገራቱ መካከል ያለው የንግድ ልውውጥም ከፍ ወዳለ ደረጃ እንዲሸጋገር የሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ሊጠናከር እንደሚገባም አመልክተዋል።

በኢትዮጵያ የማልታ አምባሳደር ሮላንድ ሚካሌፍ በበኩላቸው ኤክስፖው በኢትዮጵያ ያሉ ዘርፈ ብዙ ለውጦች በተግባር የታየበት መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ አምራቾች የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማሳካት ቁርጠኛ መሆናቸውን ያረጋገጥኩበት ኤክስፖ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ እድገት ቀጣይነት ያለው መሆኑንም መገንዘብ መቻላቸውን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የሱዳን ሪፐብሊክ ምክትል አምባሳደር ኤልሀፊዝ ኢሳ አብደላ፤ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አብዮት ለሁላችንም ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል።

ሙሉ በሙሉ የሀገር ውስጥ ምርቶች የቀረቡበት ግዙፍ ኤክስፖ መዘጋጀቱም ኢትዮጵያ ትክክለኛ የእድገት ጉዞ ላይ መሆኗን አመላካች መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026