
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦ 21 የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ(ኮሜሳ) አባል ሀገራት የሚሳተፉበት ስድስተኛው ሴት የስራ ፈጣሪዎች የንግድ ትርዒትና ኮንፍረንስ በአዲስ አበባ ተከፍቷል።
የንግድ ትርዒቱን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀመንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ እና የአፍሪካ ህብረትና የኮሜሳ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በይፋ አስጀምረዋል።
በስካይ ላይት ሆቴል የተከፈተው የንግድ ትርዒትና ኮንፍረንስ ዛሬን ጨምሮ ለሶስት ቀናት እንደሚቆይ ተገልጿል፡፡
መርኃ ግብሩ ለኢትዮጵያውያን ሴት የስራ ፈጣሪዎች መነቃቃት የሚፈጥርና ምርቶቻቸውን ለማስተዋወቅ እንዲሁም የገበያ ትስስር ለመፍጠር እንደሚያግዝ ተመላክቷል፡፡
የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ(ኮሜሳ) 21 አባል ሀገራትን የሚያሳትፈው መርኃ ግብር አዳዲስና ትላልቅ የፈጠራ ሃሳቦችን ለማስተዋወቅና ለመጠቀም እንደሚረዳም ታምኖበታል፡፡
በንግድ ትርዒቱ ከ200 በላይ ሴት ስራ ፈጣሪዎች ስራዎቻቸውንና ምርቶቻቸውን እንዳቀረቡ ተጠቁሟል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026