
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦ 21 የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ(ኮሜሳ) አባል ሀገራት የሚሳተፉበት ስድስተኛው ሴት የስራ ፈጣሪዎች የንግድ ትርዒትና ኮንፍረንስ በአዲስ አበባ ተከፍቷል።
የንግድ ትርዒቱን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀመንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ እና የአፍሪካ ህብረትና የኮሜሳ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በይፋ አስጀምረዋል።
በስካይ ላይት ሆቴል የተከፈተው የንግድ ትርዒትና ኮንፍረንስ ዛሬን ጨምሮ ለሶስት ቀናት እንደሚቆይ ተገልጿል፡፡
መርኃ ግብሩ ለኢትዮጵያውያን ሴት የስራ ፈጣሪዎች መነቃቃት የሚፈጥርና ምርቶቻቸውን ለማስተዋወቅ እንዲሁም የገበያ ትስስር ለመፍጠር እንደሚያግዝ ተመላክቷል፡፡
የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ(ኮሜሳ) 21 አባል ሀገራትን የሚያሳትፈው መርኃ ግብር አዳዲስና ትላልቅ የፈጠራ ሃሳቦችን ለማስተዋወቅና ለመጠቀም እንደሚረዳም ታምኖበታል፡፡
በንግድ ትርዒቱ ከ200 በላይ ሴት ስራ ፈጣሪዎች ስራዎቻቸውንና ምርቶቻቸውን እንዳቀረቡ ተጠቁሟል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025