
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦ 21 የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ(ኮሜሳ) አባል ሀገራት የሚሳተፉበት ስድስተኛው ሴት የስራ ፈጣሪዎች የንግድ ትርዒትና ኮንፍረንስ በአዲስ አበባ ተከፍቷል።
የንግድ ትርዒቱን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ሊቀመንበር አምባሳደር ሳልማ ማሊካ እና የአፍሪካ ህብረትና የኮሜሳ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በይፋ አስጀምረዋል።
በስካይ ላይት ሆቴል የተከፈተው የንግድ ትርዒትና ኮንፍረንስ ዛሬን ጨምሮ ለሶስት ቀናት እንደሚቆይ ተገልጿል፡፡
መርኃ ግብሩ ለኢትዮጵያውያን ሴት የስራ ፈጣሪዎች መነቃቃት የሚፈጥርና ምርቶቻቸውን ለማስተዋወቅ እንዲሁም የገበያ ትስስር ለመፍጠር እንደሚያግዝ ተመላክቷል፡፡
የምስራቅና ደቡባዊ አፍሪካ የጋራ ገበያ(ኮሜሳ) 21 አባል ሀገራትን የሚያሳትፈው መርኃ ግብር አዳዲስና ትላልቅ የፈጠራ ሃሳቦችን ለማስተዋወቅና ለመጠቀም እንደሚረዳም ታምኖበታል፡፡
በንግድ ትርዒቱ ከ200 በላይ ሴት ስራ ፈጣሪዎች ስራዎቻቸውንና ምርቶቻቸውን እንዳቀረቡ ተጠቁሟል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026