
አዲስ አበባ፤ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የግሉ ዘርፍ በመድኃኒት አቅርቦት ላይ ያለውን ተሳትፎ እንዲያድግ ያስቻለ መሆኑን የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ገለፀ።
ኢትዮጵያ ከሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ትግበራ መግባቷ ይታወቃል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የውጭ ምንዛሬ መዛባትን ማስተካከልና የረጅም ጊዜ የውጭ ክፍያ ሚዛን ጉድለትን መፍታት፣ የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፉን በማዘመን የዋጋ ንረትን መቀነስን ዓላማ ያደረገ ነው።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራው ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተለያዩ ዘርፎች ለውጦች እንዲመዘገቡ እያደረገ ይገኛል።
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብድልቃድር ገልገሎ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ከዚህ ቀደም በመድኃኒት አቅርቦት ዘርፍ ያለው የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ አነስተኛ ነበር።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የውጭ ምንዛሬ እጥረት ችግርን ለመፍታት የሚያስችልና የአምራቾችን ተወዳዳሪነት የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል።
ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ እያደገ መምጣቱን በመግለፅ።
የአገር ውስጥ አቅራቢዎች ቁጥር ከፍ እያለ መምጣቱን ተናግረው፤ ይህም ኢትዮጵያ በራስ አቅም መድኃኒት የምታቀርብበት ስርዓት መፍጠር እያስቻለ ነው ብለዋል።
ተቋሙ የህግ ማሻሻያና የሪፎርም ስራዎችን እየተገበረ መምጣቱ ከመድኃኒት አቅርቦት ጋር የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመፍታት እድል እየፈጠረለት መሆኑን ተናግረዋል።
የመድኃኒት ፍላጎት ውል በተገባለት የአቅርቦት ስርዓት ለመምራት በተጀመረው ስራ ሳይቆራረጥ ለማቅረብ የሚያስችል የሶስት አመት ውል መገባቱንም ገልፀዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025