
አዲስ አበባ፤ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የግሉ ዘርፍ በመድኃኒት አቅርቦት ላይ ያለውን ተሳትፎ እንዲያድግ ያስቻለ መሆኑን የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ገለፀ።
ኢትዮጵያ ከሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ትግበራ መግባቷ ይታወቃል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የውጭ ምንዛሬ መዛባትን ማስተካከልና የረጅም ጊዜ የውጭ ክፍያ ሚዛን ጉድለትን መፍታት፣ የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፉን በማዘመን የዋጋ ንረትን መቀነስን ዓላማ ያደረገ ነው።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራው ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተለያዩ ዘርፎች ለውጦች እንዲመዘገቡ እያደረገ ይገኛል።
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብድልቃድር ገልገሎ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ከዚህ ቀደም በመድኃኒት አቅርቦት ዘርፍ ያለው የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ አነስተኛ ነበር።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የውጭ ምንዛሬ እጥረት ችግርን ለመፍታት የሚያስችልና የአምራቾችን ተወዳዳሪነት የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል።
ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ እያደገ መምጣቱን በመግለፅ።
የአገር ውስጥ አቅራቢዎች ቁጥር ከፍ እያለ መምጣቱን ተናግረው፤ ይህም ኢትዮጵያ በራስ አቅም መድኃኒት የምታቀርብበት ስርዓት መፍጠር እያስቻለ ነው ብለዋል።
ተቋሙ የህግ ማሻሻያና የሪፎርም ስራዎችን እየተገበረ መምጣቱ ከመድኃኒት አቅርቦት ጋር የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመፍታት እድል እየፈጠረለት መሆኑን ተናግረዋል።
የመድኃኒት ፍላጎት ውል በተገባለት የአቅርቦት ስርዓት ለመምራት በተጀመረው ስራ ሳይቆራረጥ ለማቅረብ የሚያስችል የሶስት አመት ውል መገባቱንም ገልፀዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026