
ቦንጋ፣ግንቦት 4 /2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አመራሩ በየዘርፉ የተገኙ ድሎችን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር መትጋት እንዳለበት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) አስገነዘቡ።
"የመሐሉ ዘመን ወጥመድ መሻገር" በሚል መሪ ሀሳብ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)ና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በቦንጋ ከተማ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።
ኢንጅነር ነጋሽ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፥ አመራሩ በየዘርፉ የተገኙ ድሎችን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር መትጋት አለበት።
አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን በማጠናከር ከህዝቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት እርካታ ማሳደግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ሁልጊዜ አዳዲስ ሀሳቦችን በማፍለቅና ተግባራዊ በማድረግ ለተደማሪ ስኬት መትጋትና ውጤት ማስመዝገብ እንደሚያስፈልግ አንስተው፥ በዚህም የህብረተሰብን ተጠቃሚነት በተጨባጭ ለማረጋገጥ ጥረቱ መጠናከር አለበት ብለዋል።
የክልሉ አመራር በተለይም የኑሮ ዉድነትን ለማርገብና ስራ እድል ፈጠራን ለማጠናከር አቅሙን አሟጦ መጠቀም እንዳለበት አመልክተዋል።
የሚያጋጥሙ የመሐል ዘመን ፈተናዎችን በጽናት በመሻገር ወደ ብልጽግና የሚደረገውን ጉዞ ማጠናከር ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ናቸው፡፡
የክልሉ የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ መቱ አኩ፣ ተግዳሮቶችን ለማለፍ ውጤት ላይ መሰረት አድርጎ መስራት እንደሚገባ አመልክተው፥ ለዚህም የልማት ኢንሼቲቮች ዉጤታማነትን ማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመፍታት የውስጥ አሰራር ላይ በማተኮር ፈጣን ምላሽ ለመስጠት መረባረብ እንደሚገባም ተናግረዋል።
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026