
ቦንጋ፣ግንቦት 4 /2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አመራሩ በየዘርፉ የተገኙ ድሎችን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር መትጋት እንዳለበት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) አስገነዘቡ።
"የመሐሉ ዘመን ወጥመድ መሻገር" በሚል መሪ ሀሳብ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)ና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በቦንጋ ከተማ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።
ኢንጅነር ነጋሽ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት፥ አመራሩ በየዘርፉ የተገኙ ድሎችን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር መትጋት አለበት።
አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን በማጠናከር ከህዝቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት እርካታ ማሳደግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ሁልጊዜ አዳዲስ ሀሳቦችን በማፍለቅና ተግባራዊ በማድረግ ለተደማሪ ስኬት መትጋትና ውጤት ማስመዝገብ እንደሚያስፈልግ አንስተው፥ በዚህም የህብረተሰብን ተጠቃሚነት በተጨባጭ ለማረጋገጥ ጥረቱ መጠናከር አለበት ብለዋል።
የክልሉ አመራር በተለይም የኑሮ ዉድነትን ለማርገብና ስራ እድል ፈጠራን ለማጠናከር አቅሙን አሟጦ መጠቀም እንዳለበት አመልክተዋል።
የሚያጋጥሙ የመሐል ዘመን ፈተናዎችን በጽናት በመሻገር ወደ ብልጽግና የሚደረገውን ጉዞ ማጠናከር ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ናቸው፡፡
የክልሉ የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ መቱ አኩ፣ ተግዳሮቶችን ለማለፍ ውጤት ላይ መሰረት አድርጎ መስራት እንደሚገባ አመልክተው፥ ለዚህም የልማት ኢንሼቲቮች ዉጤታማነትን ማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመፍታት የውስጥ አሰራር ላይ በማተኮር ፈጣን ምላሽ ለመስጠት መረባረብ እንደሚገባም ተናግረዋል።
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026
ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...
Feb 24, 2025