የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በሀገሪቱ ባለው እምቅ የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ተጠቃሚነትን ለማሳደግ የግል ባለሃብቱ የኢንቨስትመንት ተሳትፎ መጎልበት ይኖርበታል

May 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2017(ኢዜአ)፦ በሀገሪቱ ባለው እምቅ የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ተጠቃሚነትን ለማሳደግ የግል ባለሃብቱ የኢንቨስትመንት ተሳትፎ መጎልበት እንዳለበት የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ።

በኢትዮጵያ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ባሉ እምቅ የኢንቨስትመንት አማራጮች የግል ባለሀብቱ በስፋት ቢሰማራ ተጠቃሚ እንደሚሆንም ነው ሚኒስቴሩ ያመላከተው፡፡


ግብርና ሚኒስቴር ከዓለም አቀፍ እንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩትና ከዓለም ዓቀፍ የግብርና ጥናት አማካሪ ግሩፕ ጋር በመቀናጀት በኢትዮጵያ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ኢንቨስትመንት ላይ ያተኮረ መጽሐፍን የማስተዋወቅ መርሃ ግብር ተካሂዷል፡፡

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ እንዳሉት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነ እምቅ የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ባለቤት ነች፡፡

የእንስሳትና ዓሳ ሃብት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማስፋት፣ ለግብርና ስራና ለኢንቨስትመንት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የዜጎችን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝም አመላክተዋል፡፡

በሀገሪቱ እምቅ የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ቢኖርም ከዘርፉ የሚገኘው ጥቅም አነስተኛ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይ ይህን ለማሳደግ የግል ባለሃብቱ የኢንቨስትመንት ተሳትፎ መጎልበት እንዳለበት ነው የገለጹት።

በኢትዮጵያ በእንስሳትና ዓሳ ሃብት ዘርፍ ያለውን የኢንቨስትመንት አቅምና አማራጮችን ላይ ያተኮረ መጽሐፍ መዘጋጀቱ የባለሃብቱን ግንዛቤ ለማጎልበት እንደሚያግዝም ተናግረዋል።

በግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና ዓሳ ኢንቨስትመንትና ምርት ግብይት ዴስክ ኃላፊ ከድር ሉባንጎ በበከላቸው፤ መጽሐፉ ኢትዮጵያ በመኖ ምርት፣ በማር፣ በዓሳ እና በተለያዩ እንስሳት ሀብቶች ያላትን ፀጋዎች በሙሉ ያካተተ ነው ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የሆለታ ግብርና ምርምር ማዕከል የእንስሳት ዝሪያ ማሻሻያ ተመራማሪ ዶክተር ተመስገን ጀምበር፤ በመጽሐፉ ዝግጅት ላይ መሳተፋቸውን ገልጸው፤ በመጽሐፉ ውስጥ የተለያዩ ሀገራትን ተሞክሮ በመቀመር ለኢትዮጵያ በሚመች መልኩ ማዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ያለው የእንስሳት ምርትና እርባታ በአርሶና አርብቶ አደሩ ላይ ብቻ የተመሰረተ መሆኑን አስታውሰው፤ መጽሐፉ ባለሀብቶች በዘርፉ ባሉ ምቹ ዕድሎች ዙሪያ መረጃዎችን እንዲያገኙና እንዲሳተፉ የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ስጋ አምራችና ላኪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ከሊፋ ሁሴን በበኩላቸው የማህበሩ አባላቶች ስጋን ወደ ውጭ በመላክ ሀገሪቱ ከስጋ ምርት ማግኘት የሚገባትን የውጭ ምንዛሬ እንድታገኝ እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ሆኖም ግን አልፎ አልፎ እንስሳት አቅርቦት ችግር መኖሩን ጠቅሰው አሁን የተዘጋጀው መጽሐፍ በዘርፉ ያሉትን ክፍተቶች በመፍታት በኩል አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡

እንደ ግልም ሆነ እንደ ማህበር በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ለመሰማራት ማቀዳቸውንም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026