የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የአዳማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን 26 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ ተኪ ምርቶችን አመረተ

May 15, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ የአዳማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 26 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ ተኪ ምርቶች ማምረቱን የልዩ ዞኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጉልላት አበበ ገለፁ።

በልዩ ዞኑ ተመርተው ወደ አውሮፓና መካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ከተላኩ የተለያዩ ምርቶች ከ12 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱም ተገልጿል።

የአዳማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጉልላት አበበ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት በሀገሪቱ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መደረጉን ተከትሎ ዞኑ የሪፎርም ስራዎችን ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል።

ከለውጥ ስራዎቹ መካከል ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካትና በሽያጭ ሰንሰለት ውስጥ ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል ለመፍጠር ትኩረት መሰጠቱን ጠቅሰዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ 24 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚያወጡ ተኪ ምርቶች ለማምረት ታቅዶ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ በዞኑ 26 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ተኪ ምርቶችን በማምረት ከእቅድ በላይ ማሳካት መቻሉን አስረድተዋል።

ለውጤቱም የማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ ማበረታቻዎች በአግባቡ በመተግበራቸውና የተለያዩ ማሽነሪዎችን በማስገባት ምርት ሊመረት በመቻሉ መሆኑን አስረድተዋል።

ቀደም ሲል በአልባሳት ስፌት እና ጨርቃጨርቅ ላይ ስናተኩር ከነበረው ባሻገር ለኮንስትራክሽን ግብዓት የሚያገለግሉ ተኪ ምርቶች በስፋት በዞኑ እየተመረቱ ነው ብለዋል።

ከዚህ አንፃር በፊት ከቻይና፣ ከመካከለኛው ምስራቅና ከአውሮፓ ሀገራት ሲገቡ የነበሩና አሁን በዞኑ እየተመረቱ ካሉ ተኪ ምርቶች መካከል የፕላስቲክ ውጤቶች እንዲሁም በኤክስፖርት ደረጃ የሚመረቱ የግድግዳ ቀለሞችና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች በስፋት እየተመረቱ መሆኑንም ተናግረዋል።

በዞኑ የሚገኙ ኩባንያዎች ከውጭ የሚያስገቡትን ጥሬ ግብዓቶችንም በሀገር ውስጥ ምርት እንዲተኩ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

በውጭ ምንዛሬ ግኝት ረገድም በዞኑ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ተመርተው ወደ ውጭ ከተላኩ አልባሳትና ጨርቃጨርቅን ጨምሮ ከልዩ ልዩ ምርቶች 12 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱንም ገልጸዋል።

የአዳማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ለ9 ሺህ ዜጎች ቀጥተኛ የስራ እድል የፈጠረ ሲሆን 20ሺህ ሰዎች ደግሞ በተዘዋዋሪ የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉን ጠቅሰዋል።

በልዩ ዞኑ 19 ሼዶችን በመረከብ ሥራ ላይ ከሚገኙ ኩባንያዎች መካከል ሰባቱ የውጭ ሀገር ባለሀብቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።

በአዳማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ከሚገኙ ኩባንያዎች መካከል የኖርዌይ ጆቱን-ኢትዮጵያ ካምፓኒ ተወካይ ዮሐንስ አለነ በሰጡት አስተያየት ኩባንያው የግድግዳ ቀለሞችን በማምረት ለሀገር ውስጥ ገበያ በስፋት እያቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጣር ባለፉት አራት ዓመታት ምርታማነቱን በየዓመቱ በማሳደግ ከውጭ የሚገባውን ተመሳሳይ ምርት በማስቀረት በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት መቻሉን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026

<p>ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በቦንጋ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው</p>

ቦንጋ ፤የካቲት 16/2017 (ኢዜአ) ፡-በቦንጋ ከተማ የተካሄደውን የህዝብ ውይይት የመሩ ከፍተኛ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በከተማው የተለያዩ የልማት ...

Feb 24, 2025