የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የአዳማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን 26 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ ተኪ ምርቶችን አመረተ

May 15, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ የአዳማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 26 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ ተኪ ምርቶች ማምረቱን የልዩ ዞኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጉልላት አበበ ገለፁ።

በልዩ ዞኑ ተመርተው ወደ አውሮፓና መካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ከተላኩ የተለያዩ ምርቶች ከ12 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱም ተገልጿል።

የአዳማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጉልላት አበበ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት በሀገሪቱ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መደረጉን ተከትሎ ዞኑ የሪፎርም ስራዎችን ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል።

ከለውጥ ስራዎቹ መካከል ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካትና በሽያጭ ሰንሰለት ውስጥ ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል ለመፍጠር ትኩረት መሰጠቱን ጠቅሰዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ 24 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚያወጡ ተኪ ምርቶች ለማምረት ታቅዶ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ በዞኑ 26 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ተኪ ምርቶችን በማምረት ከእቅድ በላይ ማሳካት መቻሉን አስረድተዋል።

ለውጤቱም የማክሮ ኢኮኖሚው ማሻሻያ ማበረታቻዎች በአግባቡ በመተግበራቸውና የተለያዩ ማሽነሪዎችን በማስገባት ምርት ሊመረት በመቻሉ መሆኑን አስረድተዋል።

ቀደም ሲል በአልባሳት ስፌት እና ጨርቃጨርቅ ላይ ስናተኩር ከነበረው ባሻገር ለኮንስትራክሽን ግብዓት የሚያገለግሉ ተኪ ምርቶች በስፋት በዞኑ እየተመረቱ ነው ብለዋል።

ከዚህ አንፃር በፊት ከቻይና፣ ከመካከለኛው ምስራቅና ከአውሮፓ ሀገራት ሲገቡ የነበሩና አሁን በዞኑ እየተመረቱ ካሉ ተኪ ምርቶች መካከል የፕላስቲክ ውጤቶች እንዲሁም በኤክስፖርት ደረጃ የሚመረቱ የግድግዳ ቀለሞችና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች በስፋት እየተመረቱ መሆኑንም ተናግረዋል።

በዞኑ የሚገኙ ኩባንያዎች ከውጭ የሚያስገቡትን ጥሬ ግብዓቶችንም በሀገር ውስጥ ምርት እንዲተኩ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

በውጭ ምንዛሬ ግኝት ረገድም በዞኑ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ተመርተው ወደ ውጭ ከተላኩ አልባሳትና ጨርቃጨርቅን ጨምሮ ከልዩ ልዩ ምርቶች 12 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱንም ገልጸዋል።

የአዳማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ለ9 ሺህ ዜጎች ቀጥተኛ የስራ እድል የፈጠረ ሲሆን 20ሺህ ሰዎች ደግሞ በተዘዋዋሪ የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉን ጠቅሰዋል።

በልዩ ዞኑ 19 ሼዶችን በመረከብ ሥራ ላይ ከሚገኙ ኩባንያዎች መካከል ሰባቱ የውጭ ሀገር ባለሀብቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።

በአዳማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ከሚገኙ ኩባንያዎች መካከል የኖርዌይ ጆቱን-ኢትዮጵያ ካምፓኒ ተወካይ ዮሐንስ አለነ በሰጡት አስተያየት ኩባንያው የግድግዳ ቀለሞችን በማምረት ለሀገር ውስጥ ገበያ በስፋት እያቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጣር ባለፉት አራት ዓመታት ምርታማነቱን በየዓመቱ በማሳደግ ከውጭ የሚገባውን ተመሳሳይ ምርት በማስቀረት በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት መቻሉን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026